• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አልመች አለው ጎኔ!”

May 3, 2015 08:59 pm by Editor Leave a Comment

ጥበብ የማህበረሰቡ ሁለንተናዊ ስሜት የሚገለጽባቸው ቀዳሚው እያዝናና የሚያስተምር ዘርፍ ቢሆንም አሁን አሁን ግን ያ እየሆነ አይታይም። የማፍር፣ የምኮራባቸው ጥበበኞች ጉዳይ  አሁን አሁን ያሳስበኝ ይዟል … እናም የጎልማሳው አቀንቃኝ  የጃኪ “አልመች አለው ጎኔ!” ጣዕመ ዜማ ውስጥ ስሜቴን ቢነካካው፣ የማፍር የምኮራባቸው፣ ጥበበኞች … ብየ ጀመርኩት!

የጥበብ ሰዎች በግል እንደ ተራ ዜጋ የፈቀዱትን ፖለቲካ አቋም  የመያዝ መብታቸውን የማከብር ቢሆንም ታዋቂነታቸውን ተጠቅመው ከእውነተኛ የህዝብ መብት ጥያቄና ስሜት ሳይሆን ለሆዳቸው ሲያድሩ ማስተዋል ስሜትን ይጎዳል። በተለይም ደግሞ የጥበብ ሰዎች ለሆዳቸው አድረው ከገዥ አንባገነኖች ጋር ወግነው የህዝብ ድምጽ ሳይሆን የፖለቲካ ፖርቲዎች ቱልቱላ ሲሆኑ ማየት ያማል።

ያለመታደል ሆኖ በእኛ ኢትዮጵያ ከጥቂት የጥበብ ሰዎች በስተቀር አብዛኛው የጥበብ ሰዎች ከህዝብ እውነት የራቁ  አዎዛጋቢ ሰብዕና ያላቸው እየሆኑ ነው። የሀገሬውን መከራ፣ ስቅየትና የኑሮ ውጣ ውረድ ገባ ብለው መግለጹ ቀርቶ ሲገፋና ሲበደል እንኳ አጋርህ ነህ የማይሉት አሳፋሪዎችም እየሆኑ ለመምጣታቸው ብዙ ያየነው በሊቢያ በሰሞነኛውን የISIS ጥቃትን ተከትሎ የታዘብነው አቋም ነው። ሀገር ሲያዝን፣ የሀገሬውን መከራ፣ ስቅየትና የኑሮ ውጣ ውረድ ከፍቶ መጠን ሲለቅ፣ ህዝብ ከአድማስ አድማስ ሲጨነቅ በሀዘን በመከራው ወቅት ትክክለኛውን የህዝብ ስሜት የተጋሩና የገለጹት ምንኛ የታደሉ ናቸው? በአንጻሩ ጥበብ አጓጉል ክብርን፣ ገንዘብ ለማግበስበሻነትና ለፖለቲካ ወገንተኝነት አድርገውትና አግድመው ለፖለቲካው አድልተው የህዘብን ጉዳት ያልተሰማቸው፣  ድምጻቸውን ያላሰሙት ምንኛ ያልታደሉ ናቸው?

ብቻ ጥበብ የህዝብ ስሜት መገለጫ ጭምር ናትና የህዝብ ጥበበኛ መሆን መቻል መታደልም ጭምር ይመስለኛል። ይህ እውን ሲሆን ማየትም ደስ ይለኛል ፣ ደስ ይለናል …

“አልመች አለው ጎኔ!” ይለናል ጃኪ … የውስጥ ህመማችን በሚማርክ  የድምጽ ቅላጼው አልመች፣ አልደላን ማለቱን  ሲገልጸው … ለማለዳ ወጌ መነሻ መድረሻ የሆነኝም ይህው ነጠላ ዜማ ነው፣  እኔ ወድጀለታለሁ …!

አልመች አለው ጎኔ
============
እዳክራለሁ እኔ
እዳስሳለሁ እኔ፣
ወጥቸም አልተሳካ፣
በቤቴም ሆዳ አይሞላ፣
ይሄ ሲሄድ ያ ይመጣል
ጊዜ ሽሮ ቃል ያነባል፣
አልመች አለው ጎኔን!

አንዱ ጊዜ አልፎ ጸና
ነገ እንደ ዛሬ ገና
ምድር ከሰማይ ርቃ
አንዱ ሲሄድ አንዱ ይመጣል
ጊዜ ሽሮ ቃል ያነባል፣

እዚህም ሲያልቅ ወገኔ
ማየት ተሳነው አይኔ
በቁሙ ነፍሱን ሲያጣ
እንዴት ደራሽ እንጣ?
አረ ጉድ ነው አቤት ቁጣ!
ሀሰት  እውነት  ሁኖ  እየኖረ
ስንቱ ኑሯል  እያማረረ

ተስፋው፣ ሲጨልምበት
ነፍሱን ሰጠ፣ ለስደት

አይነጋም ወይ? ያ ጨለማ
አለው በይን  አንች  እማማ!
አልመች አለው ጎኔን!

ደርሶ የሞላ እለቱ
በዘመድ በጥረቱ
ተረሳ የትናንቱ
ከፍ ስላለ ቤቱ

ጉርሻ አምጣ
አለው ጣጣ
በዚህ ቁጣ
ለውጥ የት ይምጣ?

ጣፋሽ  ስኳር ስትልስ
ኑረሃል አንተ ምላስ
ይበቃሃል ሀቁ ይውጣ
የላዩም አይቆጣ
ፍርድ የላይ ነው ምድር ከንቱ
ይበጀናል እንደ ጥንቱ

ሳቅ ሳቅ ሲለኝ
ዝም አንች አያፍርም
ስቅ ሲለኝ
ውሃ ዘግ የለም

ብዙ ሚሊዮን ቆጥሮናል
መስማማት አቅቶናል

ማን በቤቱ አርፎ ይተኛ
ሰው በሰው ቤት ሆኖ አድመኛ

አልመች አለው ጎኔን
ርቆ እንደሰማይ ከኔ
አልመች አለው ጎኔን …

****  ****** ******
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ነቢዩ ሲራክ
ሚያዝያ 22 ቀን 2007 ዓም

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule