• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንዴት እንኑር!

August 10, 2013 11:48 pm by Editor Leave a Comment

… ለመሆኑ ከየት መጣን?…. ወዴት እንሄዳለን? …እንዴትስ እንኑር? የሚሉትን የፈላስፋውን ጥያቄ ስናነሳ፣ ግሪክ አገር አቴን ከተማ የዓለም ፈላስፋዎች ሰሞኑን ተሰብስበው “ስለ ዓለም ሁኔታ ይነጋገራሉ” ብለን አልገመትንም ነበር።

እኛ በዚህ እትማችን ሰለ ዓለም ሳይሆን ስለ እኛው ስለ ራሳችን ችግር ነው አንዳንድ ነገሮቸን አንስተን ከግንዛቤ ውስጥ አስገብትን መለስ ብለን ለመመልከት የተነሳነው።

“…እንዴት እንኑር? ” የሚለው ጥያቄ ሲሰነዘር የሚያስቆጣቸው ሰዎች እንደሌሉ ተስፋ እናደርጋለን።

አንደንድ ጊዜ ከረጅም መላ-ምትና ግራ ከሚያጋቡ ጠማማ ጽንሰ-ሓሳቦች፣ ከቲዎሪ ዎች ይልቅ ቀላልና ጥሩ ጥያቄ ማቅረብ ፣ሌላውም ጎረቤት አገር ሆነ ራቅ ያሉ ሰዎች “እነሱስ እንዴት ይኖራሉ ?”ብሎ እራስን መጠየቅ ከብዙ ድካምና መነከራተት ያድናል።

ግን ደግሞ ወደፊት ዘልቃችሁ እንደምታነቡት ፣ እንደዚህ ዓይነቱ አካሄድ ደግሞ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት በደንብ ከአልተወያዩበት የአርባና የሃምሳ አመት መከራ ውስጥ አንድን ሕዝብ ከቶ አገሪቱን ያተረማምሳል። እንኳን እኛ “እንዴት እንኑር ?” ብለን ከሩሲያ በተዋስነው ትምህርት “በቀላሉ ነጻ ልንወጣ” ቀርቶ ራሺያ እራሱዋ ከገባችበት ማጥ ለመውጣት ከሰባ አመት በላይ ፈጅቶበታል ።

“…እንዴት እንኑር? ወዴት እንሄዳለን? ከየት መጣን ” የሚለው ጥያቄ የፈላስፋዎች ጥያቄ -ወረድ ብለችሁ እንደምታዩት- ብቻ አይደለም። ግን አንድ ክፍል ከሌላው በልጦ፣ የግንባር ቀደምነት ቦታውን ይዞ “…እኔ ያልኩት ከአልሆነ፣ ሞቼ እገኛለሁ፣ አለበለዚያ ዋ! አንተ ከአልተቀበልክ፣ እኔ አንተን እገደልሃለሁ…” የሚል የምሁር ክፍል አለ። እሱ ነው እንግዲህ የእኛ የዛሬው እትማችን አርዕስት።

ምሁሩ በጅምላ ሲታይ በሕብረተሰቡ ውስጥ ጥቂት አይደለም። እነሱም በተለያዩ መስኮች ውስጥ ተሰማርተው እራሳቸውንም ሕብረተሰቡንም፣ አገሪቱንም ቤተሰቦቻቸውን በአእምሮ ሥራቸውና ችሎታቸው ይረዳሉ ። ግን ከእነሱ አንዱ ክፍል -ቀጥሩ ትንሽ ቢሆነም- በጩኸቱ፣ በክርክሩ፣ በጽሑፉ፣ ግርግር በመፍጠሩ፣ በክሱ፣ በብዕሩና በምላሱ፣ በመቀስቀስና በማደረጀት ችሎታው፣ በአፍዝ አደንግዝነቱ…ጠቅላላውን መድረክ በመያዝ ችሎታው ማንም የሚደርስበት የለም። እሱም “አቫንጋርዱ የሙያ አብዮተኛ ” የሚባለው ትንሽ ክፍል ነው።

ይህ ክፍል (ፖለቲካ ምንድነው ? በሚለው መጣጥፍ ላይ አንሰተናል) ለሠራውና ለሚሰራው ሥራ ኃላፊነትና ተጠያቂነት እማይሳማው ነው። በዚህም ከሌሎች ሕግ አክባሪ ፖለቲከኞች ፍጹም ይለያል።

ኃላፊነት መቀበል ምንድነው? በአጭሩ “ሁሉን ነገር ማድረግ ስችል ለምን አላደርገውም “ብሎ መነሳት ነው። ሃምሳ ሚሊዮን፣ ሰባ ና ሰማኒያና ከዚያም አልፎ ዘጠና ሚሊዮን በሚኖርበት አገር፣ አምስትም ሚሊዮን ይሁኑ “….ጥቂት ሰወች ተሰባስበው እኛ ለአንተና ለአንቺ፣ እንዲያውም ለሁላችሁም የአሰብነው የአኗኗር ዘይቤ ወይም ሥርዕት ይህ ነው፣ ወደዳችሁት ጠላችሁት ተቀበሉት፣ ከዚያ ወጭ ትንሽ ትንፍሽ ብትሉ…” ተብሎ ፖለቲካ የሚሰራበት ዘመን ከምሥራቁ ዲክታተሮች ጋር አብሮ አልፎአል። ይህ ጊዜም አክትሞአል።

የአሁኑ እትም አተኩሮ በአገራችን ብቻ ሳይሆን በአፍሪካና በእሲያ በሥራቅ አውሮፓም ጭምር ፣አንድ የቶታሊቴሪያን አስተሳሰብ እንዴት በጥቂት ምሁሮች አመካኚነት እንዴት ተስፋፍቶ እንደመጣና “የሰውን” ልብና አእምሮ ፣የእራሳቸውንም “የፈጣሪዎቹና የተከታዮቸንም ” መንፈስ ይዞ እነሱን እንዴት “አገልጋይ ባሪያቸው” እንዳደረጋቸው ከብዙ በጥቂቱ ለማሰየት ነው።

እገረ መንገዳችንን “እኛ ማነን!” የሚለውን ስለ አሜሪካን ክሬዶ ፣…አሜሪካንን አሜሪካ ስለ አደረገው ፣ መንፈስ፣ እሱ ጸሓፊው ሳሙኤል ሐንቲንግተን “እስፐሪት” ቀደም ሲል የጻፈውን መጽሓፍ ተመልክትን አጠር ያለ ግርፋትና ክትበት ሰጥተናል።

እንዴት እንኖራለን? እንዴት አብረን እንኑር ? እናውቃለን አወዛጋቢ ጥያቄ ነው። ግን በዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ መካከል “ኢሚንት የማይሞሉ የፖለቲካ ሰዎችም አጉል ቲዎሪ አንግበው፣ እኛ ያለነው ብቻ…” እያሉ መከራ ከሚያሳዩ ጠለቅ ያለ፣ ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሄድ ነገር በያቀርቡልን ደግ ነው። ያ ቲዎሪ እኮ የ19ኛው ክፍለ-ዘመን ትምህርት ነው። ከእዚያ በላይ ይህን ቲዎሪ የሚያራምዱት ከጠቅላላው የአገሪቱ ምሁሮች፣ በሌላ መስክ ላይ ከተሰማሩት ከእነሱ ጋር ሲነጻጸሩ፣ እንደዚሁ ትንሽ ናቸው።ይህንንም ማወቅ ያስፈልጋል።

ተሽከርካሪ ጎማ ገና ዱሮ ጥንት በተፈጠረበት ዓለም –አውሮፓያኖች፣ ወርቅማ ጊዜህን አዲስ ታይቶና ተሰምቶ ተሞክሮ ፣ የማይታወቅ አዲስ ተሽከርካሪ ጎማ እፈጥራለሁ ብለህ ጊዜህንም ጉልበትህንም አትጨርሰው ይላሉ። ይህም ማለት በአጭሩ አዲስ የሕብረተስብ ሞዴል፣ በዓለም ላይ ታይቶም ተሰምቶም የማይታውቅ እፈጥራለሁ ብሎ መድከም ከንቱ ነው። ያው የምናውቀው የዲምክራሲና የታወቀው የፓርላማ ሥርዓት፣ ነጻው ሕብረተሰብ ይሻለናል።

የነገሮች ሁሉ እምብርት ደግሞ፣ ወዳጄ ! ነጻ ሐሳብ፣ በነጻ-ፕሬስ ላይ ማራመድ ነው። ከሁሉም አቅጣጫ ነገሮችን ሰርስረን “እንዴት እንኑር?” ለሚለው ጥያቄ በየጊዜው መልስ እንሰጣለን።

(የ”ለአእምሮ መጽሔት” ዋና አዘጋጁ ይልማ ኃይለ ሚካኤል)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule