• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሂወት ውል /Hewett Treaty/

March 12, 2017 06:31 pm by Editor 1 Comment

የሂወት ውል በ1876 ዓ.ም (1884) አጼ ዮሐንስ ከእንግሊዝና ግብጽ ጋር ውል የገቡበት ሲሆን ንጉሱ በሰሩት የፓለቲካ ቀመር ስህተት የኢትዮጵያን ጥቅምና ሙብት አሳልፈው ለወራሪዎች የሰጡበት፣ ከጎረቤት ደርቡሾች ጋር ጠላትነት በመፍጠር ለጎንደር መተማ መውደም (በደርቡሾች መቃጠልና መዘረፍ) እንዲሁም ለራሳቸው ለዮሐንስም ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነ፣ ኢትዮጵያን እርስ በርሱ ተያያዥነት ወዳለው ችግር ውስጥ የከተተ አስጠቂ ውል ነው። ይህንን ውል ተከትሎ እንግሊዝ ምጽዋን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ባለቤት ለሆነችው ለኢትዮጵያ ማስረከብ ሲገባት ለጣሊያን አሳልፋ ሰጠቻት። ጣሊያን ሳትለፋና ሳትደክም እንደ ገና ስጦታ ከእንግሊዝ ከተበረከተላት ከምጽዋ ወደብ በመነሳት ወደ ውስጥ ሃገር ቀስ በቀስ መስፋፋት ጀመረች።

ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር ምጽዋ ላይ ስትደራጅ ብሎም ያለማቋረጥ ወደ ውስጥ ስትስፋፋ አንድ ነገር መደረግ አለበት እያሉ ራስ አሉላ በተደጋጋሚ በወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉስ ለነበሩት ለአጼ ዮሐንስ ቢያሳስቧቸውም ለቴዎድሮስ ሞትና ለዮሐንስ መንገስ ባለውለታ የሆኑትን እንግሊዞችን ላለማስቀየም እንዲሁም በፈረመት የሂወት ውል ምክንያት ሁለት እጃቸው የታሰረው አጼ ዮሐንስ ምንም ማድረግ አልቻሉም ነበር። በተለይም ራስ አሉላ አንተን አውርዶ መንገስ ይፈልጋል በማለት እንግሊዞች የሚያስወሩትን ወሬ በማመን አሉላን በማግለላቸው የተነሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጣሊያን እየተጠናከረ መጣ፣ ኢትዮጵያም የበለጠ የችግር አረንቋ ውስጥ እየገባች ሄደች።

የጣሊያኖችን የማይቆም መስፋፋት እና የንጉሱን ቸልተኝነት መታገስ ያልቻሉት ራስ አሉላ አባ ነጋ ሰሃቲ እና ዶጋሊ በሚባሉ ቦታዎች ከጣሊያኖች ጋር ጦርነት በማድረግና ወራሪውን በማሸነፍ ለጊዜው የጣሊያንን መስፋፋት የገቱት ቢሆንም ንጉሱ የሃገር ጉዳይነቱን በመተውና አሉላ ለስልጣኔ ያሰጋኛል በሚል መሠረተ ቢስ ጥርጣሬ ያለኔ ፍቃድ ለምን ከጣሊያን ጋር ጦርነት ገጠምክ ወደሚል የግል ተራ ጥል ውስጥ ገቡ። በዚህም የተነሳ ንጉሱ መቀመጫቸውን አስመራ በማድረግ እስከ ምጽዋ ድረስ በመወርወር ጣሊያንን ሲያስጨንቁ የነበሩትን ጀግናውን ራስ አሉላን ከስልጣናቸው በማንሳታቸው የተነሳ በተፈጠረ ክፍተት በመጠቀም ጣሊያኖች ያለከልካይ አስመራ ከተማ ሰተት ብለው መግባት ቻሉ።

አጼ ዮሐንስ የሰሩት ስህተት ለአጼ ምኒልክ እዳ ሆነባቸው። ስለዚህ አጼ ዮሐንስ በሰሩት ስህተት ምኒልክ ምን ያድርጉ? የትግራይ ባላባቶች ከጣሊያን በሚያገኙት አልባሌ የካኪ ሱሪና ኮት የሃገራችንን ጥቅም ለጣሊያን አሳልፈው ሲሰጡና በጥቅማ ጥቅም ሲሞዳሞዱ ጀግናው ምኒሊክ ናቸው ከሸዋ ድረስ ሺ ኪሎ ሜትር ተጉዘው ሄደው አድዋ ላይ ጣሊያንን አሸንፈው ከነጭ ባርነት ትግራይን ነጻ ያወጡት። ለምን በጣሊያን አልተገዛንም ካልሆነ በስተቀርር የሚያመዛዝኑበት ህሊና ካለቸው አጼ ምኒሊክ ለትግራይ ባለውለታ ናቸው። (Dereje Tefera የጻፈውን Bahirdar Press ፌስቡክ ላይ ታትሞ የተገኝ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    March 20, 2017 01:59 am at 1:59 am

    wei gud,men aynet asafari sewoch nachehu,derows ke mengistu zer men yemireba ywetal?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule