• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጥሩ ምግባር ሁሌም ያስመሰግናል!

August 1, 2014 03:45 am by Editor Leave a Comment

ለእኔ ለፈጣሪ በታች በጎ ለሚሰሩ የሰው ዘሮች በሙሉ የሚሰጥ ምስጋና ቃል ይስበኛል። ብዙ ጊዜ የመልካምና የበጎ ምግባር ፋና ወጊዎች ስራ ተመልክቸና መስጦኝ ለቀሪው አርአያ፣ ለወደፊቱ ብሩህ ተስፋ ምንጭ ነው ብየ ካሰብኩና ካመንኩበት የምስክርነት ቃሌን የምሰጠው ምስጋና በማቅረብ ነው።  ይህን ካልኩኝ ዘንዳ የዛሬ የእኔን ምስጋና በአስተዋሽ አመስጋኙ አይታክቴ ለፌስ ቡክ ወዳጀ Eduardo Byrono፣ ለወጣቷን ድምጻዊ  ሃኒሻ ሰሎሞን ያላቋረጠ ድጋፍ አድርጎ ለውጤት ላበቃ ጋዜጠኛ ወዳጀ ለጋዜጠኛ ድልነሳው ጌታነህ እና ለድምጻዊ ሃኒሻ እጅ በመንሳት ምስጋና በማለዳ ወጌ ላቀርብ በቀኝ ጎኔ ተነስቻለሁ!

ዘመኑ ረቅቋል፣ ጊዜ ወስደን የምናዘጋጃቸውን ማናቸውም መረጃዎቸ በሰከንድ ልዩነት ከአንዱ ከአድማስ አድማስ መርጨት በቀለለበት ዘመን ላይ እንገኛለን። በማህበራዊ ድህረ ገጾች  የሚተላለፉ ያልረባቡ ዝባተሎ መረጃዎች እንዳሉ ሆኖ ለሰው ልጅ አስተሳሰብ እድገት ጠቀሜታ ጉልህ ሚና ያላቸው መረጃዎችም ይቀርባሉ። ስለ ሰው ልጅ ፍቅር፣ ሰላም፣ ህብረት፣ ሰብአዊነት ብሎም ስለምኖርባት አለምና ወረድ ሲልም eduardoስለ ሃገር ሰፊና ጥልቀት ያለላቸው ምርመሮችና ጥናቶች እንማርባቸው ዘንድ በሰፊው የመረጃ መረቡ ይስተናገዳሉ። የታደሉት ብጹአን ተመራማሪዎች የምርምር ስራቸውን ሲያቀርቡ መረጃውን በማቅረብና በማሰራጨት የተሰማሩ ብጹአንም መረጃ መርጠውና አደረጃጅተው ወደ እኛ ያደርሱታል. . . ከፋናወጊወቹ የሃገር ልጆች አንዱ ደግሞ ወዳጀ ኤድዋርዶ ቡርኖ ነው …

ከፈረንጆች ተወስዶ በእኛ ሃገር ብዙም ያላዳበርነው ይህ የምስጋናና እውቅናን የመስጠት ይተበሃል አሁን አሁን በስልጡን ወጣትና ጎልማሳው ትውልድ አበረታች መንገድ እየያዘ ለመምጣቱ ኤድዋርዶ ጥሩ ምሳሌ ነው ባይ ነኝ።

ከወደ ምድረ አሜሪካን ሃገር ነዋሪ የሆነ የፊስቡክ ወዳጃ Eduardo Byrono  የምናውቀውን ጸሃይ የሞቀውን እውነት፣ እያየነው የማናሰወተውለውን፣ ይዘነው የምንኮራ፣ የማንኮራበትን፣ ግን ጠቃሚውን ሁሉ ሳይታክት እየቃረመ የሚያቀርብልን ወንድም ነው። ወዳጀ ያልሄድንበትንና ረስተነው ዝም ያልነውን የእናት ኢትዮጵያና ህዝቧን ታሪክ አበጥሮ እያስተዋወቀ ያወያየናል። የቀደሙ የተረሱ መረጃዎችን ወደኛ አስፈንጥሮ ማንነትን አብሮን ይፈልጋል፣ ያፈላልጋል። የተደበቀውን ቆፍሮ ያወጣና እውቅናና ምስጋና እንድንሰጥ ያበረታታናል። ኤድዋርዶ እንዲህ እያለ የእናት ሃገር ኢትዮጵያን ባህሏንና ወጓን፣ ጀግኖቿንና ቅርሷን ያለ መታከት ያዘክራል! ምስጋና ለወዳጃችን Eduardo Byrono ይገባል!

ጋዜጠኛውና ድምጻዊዋ …

ወዳጀ ጋዜጠኛ ድልነሳው ጌታነህ ከማመስገኔ በፊት እንዳመሰግነው ምክንያት የሆነችኝ ድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን መስከረም በጠባ ማግስት በዋሽንግተን ዲሲ ስለምታደርገው የሙዚቃ ድግስ በጨረፍታ ከዚያም ስለ እኔ ሃኒሻ ግንኙነት ጥቂት ላንሳ ….

hanisha8ተስረቅራቂ ግሩም ድምጽ ያላት ድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን በምድረ አሜሪካ የሙዚቃ ድግሷን የምታቀርብ ሲሆን የሙዚቃ ድግሱ አላማ በአፍሪቃ የሚደረገውን የመሬት ቅርምት የአፍሪቃን አህጉር ለእጅ አዙር አገዛ የሚዳርግ መሆኑን የአለም ህዝብ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ መሆኑንም ሰምቻለሁ። በታዋቂው አርቲስት በቦኖ በተዘጋጀው በዚህ የሙዚቃ ዝግጅት ሃኒሻ ግንባር ቀደም በመሆን ዝግጅትዋን ታቀርባለችም ተብሏል። በዚህ ዝግጅት ላይ “ተባበሪ አፍሪቃ!” የሚለው ዘፈኗ በመላ የእለቱ ተካፋይ አርቲስቶች በህብረት የሚዜመው በዋሽንግተን ዲሲ DAR- Constitution Hall በመጭው መስከረም 11 ወይም እአአ Sept 21 , 2014  ሲሆን የመድረኩ ጌጥ ድምጻዊት ሃኒሻን ማየት መታደል ነው።

ድምጻዊት ሃኒሻን የማውቃት ከወራት በፊት በሳውዲ ኢትዮጵያው ስደተኞች ላይ መጠነ ሰፊ ” ከሃገር ውጡልን !” የሳውዲዎችhanisha7 ወከባ በተከሰተበት ወቅት  ነው።… ትውውቃችንም እንደ ዋዛ በፊስ ቡክ ጓደኝነት ጠነከረ።  በስደተኛው ዙሪያ የማቀርባቸውን የማለዳ ወጎችን አልፎ አልፎ የምትከታተለው እህት በአሳዛኝ ታሪኮች መነካቷ አልቀረም። እናም መረጃውን ተመልክታ ዝም አላለችም። ሌላው ሁሉ ቢቀር በጅዳ ቆንስል ተጠልለው ለሚገኙ በርካታ እህቶች በግል የእርዳታ ድጋፏን ለማድረግ ቀን ተሌት ትወተውተኝ ገባች። ያም ሆኖ እርዳታውን ለማድረግ ተጠያቂነት ባለው ደረጃ የተደራጀ የእርዳታ ማሰባሰብ ባለመኖሩ ብዙም እንድትገፋበት አለመከርኳትም። ግፉአን ኢትዮጵያውያን ታመሙ እና ተጎሳቆለው በተለያዩ የሳውዲ አውራ ጎዳናዎች ወድቀው አገኛለሁ። ግፉአኑን ችግራቸውን “እህ” ብየ አደምጨ፣ ጠይቄና ፎቶ አንስቸ ላልሰሜ  የስደትን አስከፊነት ለወገኔ፣ የመብቱን ጥሰት ጠባቂ ማጣት ለሚመለከታቸው አቀርበዋለሁ። ይህንን መረጃውን የምትከታተለው ሃኒሻ “ሌላ ማድረግ ባይቻለኝ በጠራራው ጸሃይ የውሃ መግዣ ካልለሰኩላቸው!” እያለች ለወገን ያላትን ድጋፍ ከሚገልጹልኝ ወገኖች መካከል በቀዳሚነት ስለምትሰለፍ ለድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን ታላቅ አክብሮት አለኝ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከሃኒሻ ጋር አልፎ አልፎ እየተገናኘን ከማህበራዊ ኑሮው እና  አልፎም በጥበቡ ዙሪያ  እናወጋለን!

hanisha2ድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን በተለይ ከኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ሁና አማርኛን በመጫወቷ የሚቀየሟት አልጠፉም። ያም ሁሉ በጽኑ ኢትዮጵያዊ ስሜት በሙዚቃ ሰላምን ፣ ፍቅርን አንድነትና ህብረትን መፍጠር ሃገረ ሎንደን የከተመችው የወጣቷ ድምጻዊት የሃኒሻ ሰለሞን ህልም ሆኖ ቀጥሏል!

የድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን ሰብዕናና ለሃገሯ ያላት የማይቆረፍድ ህልም እንዳከብራት አድርጎኛልና ስራዋን እከታተላለሁ አደንቃለሁ። ከድምጻዊት ሃኒሻ ጋር አልፎ አልፎ በቀጭኑ መስመር ስንገናኝ በምናደርገው ጭውውት ከአፏ የማይለየው  የሙያ ባልደረባየ ጋዜጠኛ ድልነሳው ጌታነህ ነው! ሃኒሻ በስኬቷ ዙሪያ ደጋግማ ስትናገር “አባቴ ነው” የምትለው የሙዚቃ ስራዋን የሚያንቀሳቅስላት ጋዜጠኛ ድልነሳህ የተባለ ደልዳላ አለቃ አላት! ድምጻዊት ሃኒሻን “አባቴ ነው! ” ባያስባላትን ጋዜጠኛና የሙዚቃ ባለሙያ ወዳጀ በጎ የድጋፍ ስኬት ኮርቻለሁ!hanisha1

… ጋዜጠኛ ድልነሳው ከሎንደን እኔ ከሳውዲ አረቢያ በዚህና በዚያ ጫፍ ለጀርመን ራዲዮ በዘጋቢነት አብረን ሰርተናል … ሁሉ ሆኖ ድልነሳውን በደንብ የማውቀው በሃኒሻ በኩል በሚደርሰኝ መረጃ ነው!  እናም ዛሬ ለወዳጀ ምስጋና ላቅርብ!

dilnesaw
ድልነሳው

ወዳጀ እና የሙያ አጋሬ ጋዜጠኛ ድልነሳው ሆይ! … የወጣቷ ድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን ስኬት የአንተ ያላሰለሰ ብርቱ ድጋፍ ውጤት መሆኑን ድምጻዊት ሃኒሻ ሰሎሞን የምስክርነት ቃል መሆኑን ሰምቸ እንዴት ዝም ልበል? በእርግጥም የሃኒሻ መጎምራት፣ የሃኒሻ ለዚህ መብቃት፣ የሃኒሻ ስኬት ከፈጣሪ በታች የአንተ ብርቱ ድጋፍ ነውና ልትመሰገን ይገባል!  የኦሮሞ ባህሏን በኩራት ይዛ ከአማርኛና ከቀረው የሃገሯ የኢትዮጵያ ብሔር  ቋንቋ ጋር በማቀንቀን አንድነታችን ለማጎልበት ለምትደክመውን ታዳጊ ወጣት ላደረግከውና ለምታደርገው ድጋፍ ውለታ መላሹ የላይኛው ጌታ እግዚአብሔር ነው፣ እሱ ይርዳህ! እኔም ለበጎ ምግባርህ አመሰግንሃለሁ!

በመጨረሻም ብርቱ ወዳጀ ድምጻዊት ሃኒሻ ሰለሞን አንችም በሰብዕናሽና በሃገር ወዳድነትሽ ኮርቸብሻለሁ!

አመሰግንሻለሁም! በመንገድሽ ሁሉ እግዚአብሔር ይከተልሽ! ቅን ሰው ነሽና ይቅናሽ!

ከአክብሮት ጋር …

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule