• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እማይቻለው – ለተቻለው”

May 20, 2015 03:18 pm by Editor Leave a Comment

… እንዴት ነበር ከቶ ውጣ-ውረዱ…?
…ተረተር፣ ሸለቆ…፣ አቀበት፣ ቁልቁለቱ…፣
…ጉድባው፣ ጉብታው…፣ አባጣ-ጎርባጣው…፣
…እሾኽ፣ እንቅፋቱ…፣ መሰናክል፣ ምቱ…፣
…ጠመዝማዛው ጉዞ…፣ እንዴት ነው መንገዱ?

የያሬድ ልጅ ጠቢብ – መንፈስ የማኅሌታይ፣
የሰልስቱ ዜማ – ግዕዝ፣ እዝል፣ አራራይ፣
ነፍስን መሳጭ ቅኝት፣ ገነተ-ሕይወት አምሳል፣
አንቺሆዬ፣ ባቲ፣ ትዝታ፣ አምባሰል፣
ዓለም ኖታ ሳይነድፍ – የነበርንን እኛን፣
ሕዳሴ-ወጥበብ – ዳግም አስተዋውቀን፤

የ”ክፉ ቀን” ጓድህን፣ የደስታ ምንጭህን፣ የውጥን አጋርህን…
ፒያኖህን ይዘህ ምጠቅ ክበርበት፣
ውጣ ተራራውን እስክትደርስ ከጫፉ…
ከምኩራቡ ስፍራ ያምላክ ቃል ካለበት፤
ፍጹም ልቀህ ቆመህ ከዚያ ክቡር ማማ፣
የገደል ማሚቶው ዘልቆ እስከሚሰማ፣
በአምባሰል መንፈስ፣ በዕልልታ ድምጸት፣ በሰመመን ቃና…፣
መስክር ባለም ዙሪያ – ዘላለም መኖሯን ኢትዮጵያችን ገና!

ዶ – ሬ – ሚ .. ሶል – ላ .. ዶ – የሙዚቃን ሳይንስ፣
ከሽነህ ክተበው – ለሁሉ እንዲዳረስ፤
አሳየው ለትውልድ – የረቂቅ ሙዚቃን፣
የተመስጦ መንፈስ – ውብ ረቂቅነቱን፤
አርቅ፣ ቀምር፣ ዘምር…
ሕያው ጥበብ ስራ – ዘመን እሚሻገር፤

ባለዋሽንት እረኛ፣ ለአንጋፋው ክብር ዕሴት አገርኛ፣
ሰላም እና ፍቅር፣ – የርግብ መልዕክተኛ፣
ጨዋታ…፣ ዕልልታ…፣ የክብር የደስታ ምስጋና ስጦታ..፤

.. ቁልቁል በየመስኩ – የጥበብ ወንዝ ይፍሰስ፣
ጋራ-ሸንተረሩን… ለምለም መሬት ያርስ፣
ያንን ተመግበው ቁጥቋጦች ይፋፉ፣ አበቦች ይድመቁ፣
ለታታሪ ንቦች – ተስፋን ይሰንቁ፤
ለዘላለም ዓለም – ሲቆጠር ዘመኑ፣
ለዘላቂው ሕይወት – ያገር አድባር ዋርካ ሞገስ እንዲሆኑ!

ያልተቻለው – ይቻል፣ ይቀጥል ጥረቱ፣
ይሁንልን በጎ – ላገር ተምሳሌቱ!
ክበር፣ ተመንደገው – በመረጥከው ሙያ፣
ግርማ! ሞገስ ሁናት ለእማማ ኢትዮጵያ!

ጌታቸው አበራ
ግንቦት 2007 ዓ/ም
(ሜይ 2015)

ግጥሙን በPDF ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ
____________________________________________________________

ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ ገና ከጠዋቱ ጀምሮ፣ በያዘው ሙያ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ፣ እማይቻል እሚመስለው ነገር ተችሎት ዛሬ ካለበት እርከን ላይ የደረሰ እውቅ የሀገራችን ፒያኒስት (ክላሲካል ፒያኖ ተጫዋች)እና የረቂቅ ሙዚቃ ደራሲ ነው። በያዘው ሙያ ለሀገራችን ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ ላይ ከመሆኑም በላይ፣ አርአያነቱም በሁሉም መስክ ለሀገራቸው በጎ ተግባር ለመከወን ወጥነው ለተነሱ ሁሉ የሚተርፍ ነው። ስለዚህም ኢትዮጵያውያን ግርማ የጥበብ ስራዎቹን በሚያቀርብባቸው ስፍራዎች ሁሉ በመገኘት ከረቂቅ ሙዚቃ ማዕዱ ልንቋደስና ለበለጠ ስራ ልናበረታታው ይገባል እላለሁ። በዚህ አጋጣሚ ግርማ ይፍራሸዋን፣ ለጥረትህ ፍሬ በመብቃትህ እንኳን ደስ ያለህ እያልኩ፣ በጀመርከው ረዥም የዳገት ጉዞ፣ ከ’ተራራ’ው ጫፍ ላይ በመድረስ፣ ለግልህ ከፍተኛ እርካታን፣ ለሀገርህ የላቀ አበርክቶትን፣ ለወገንህ ኩራትና አልኝታነትን በላቀ ደረጃ ታጎናጽፍ ዘንድ መልካም ምኞቴንና ሙሉ ተስፋዬን ለመግለጽ እወዳለሁ።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule