• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በመንግስት አመራር ውስጥ ‘እኔ አውቅላችኋለሁ’ የሚል ደዌ ተጠናውቶን ቆይቷል” አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

August 26, 2018 10:51 am by Editor Leave a Comment

ገዱ አንዳርጋቸው በምሁራን መድረክ ያድረጉት የመክፈቻ ንግግር

  • ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
  • የተከበራችሁ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች!

እንኳን ወደ አማራ ክልል መዲና ውቢቷ ባህርዳር ከተማ በሠላም መጣችሁ!

ከነገሬ ሁሉ በማስቀደም የአማራ ክልል መንግስት እና ህዝብ የጐደለውን ትሞሉለት ዘንድ ምክራችሁን እና የሙያ ድጋፋችሁን በመሻት ለልጆቹ ያደረገውን ይህን ታሪካዊ ጥሪ ያለምንም ማቅማማት ተቀብላችሁ እዚህ በመካከላችን በመገኘታችሁ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ።

በረጅሙ የሃገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የአማራ ህዝብ በስልጣኔ፣ በተለይም በመንግስት አስተዳደር፣ በታሪክ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በስነ-ፅሁፍ፣ በአርበኝነት ተጋድሎ እንዲሁም በኢኮኖሚ ዕድገት ለሃገር ያበረከተው ድርሻ ትልቅና አይረሴ ቢሆንም ያለፈው ግማሽ ምዕተ-ዓመት በዘመናዊ ትምህርት የጐለመሰው የክልሉ ተወላጅ ቁጥሩ ከፍ እያለ የመገኘቱን ያክል ተሣትፎው ግን እየቀዘቀዘ መጥቷል።

ለዚህ ዋነኛ ምክንያቱ አሳታፊ /አካታች/ የመንግስት አስተዳደር አለመኖሩና በመንግስት አመራር ውስጥ “እኔ አውቅላችኋለሁ” የሚል ደዌ ተጠናውቶን መቆየቱ ነው። ይህ ጉዳይ በሁሉም የሙያ ዘርፍ አንቱ የሚባሉና ለሃገራችንም ሆነ ለዓለም የተረፉ ምርጥ ምሁራን ለፈለቁበት የአማራ ህዝብ “የዐባይን እናት ውሃ ጠማት” እንደሚሉት አይነት ሆኖበት ቆይቷል። በመመካከር ፈንታ መወቃቀስ፣ በመደጋገፍ ፈንታ መገፈታተር፣ በፍቅር አብሮ መሥራት እና አብሮ መብላት የአባት አደር ሆኖ ሳለ የአንድነትና ወንድማማችነት ጽዩፋን እየሆን እንገኛለን።

ለዚህ ሁሉ ችግር ተወቃሽ ባይጠፋም ወቃሽ ሆኖ መቅረብ የሚችለው ግን ትልቁ የአማራ ህዝብ ብቻ በመሆኑና የህዝባችን ዐቢይ ፍላጐትም ሁላችንም የምንችለውን ያክል ሠርተን ከችግር እንድናወጣው ሥለሆነ ዛሬ በመካከላችሁ የቆምኩት ይህንኑ ጥሪ ለማሥተላለፍ ብቻ ነው።

ወንድሞች እና እህቶች !!

መማር ማለት በርካታ መፃህፍትን ውጦ መቀመጥ ብቻ አይደለም። እንደ እውነቱ ከሆነ መማር በዩኒቨርሲቲ በሚሰጥ የሊቅነት ማረጋገጫ ወረቀት ብቻ ሊገለጥ አይችልም። በእኔ እምነት መማር የህዝብን ህመም አብሮ ታሞ መፈወስ መቻል ነው።

ትምህርት የተጨነቀን ህዝብ ከችግር ለማውጣት የሚያስችል መሣሪያ ሆኖ ካልተገኘ ልሂቃን ሲፈልጉት ብቻ የሚጠቀሙበት ተከቶ የተቀመጠ ትርፍ ሃብት ይሆናል። የክልላችን ህዝብም ይሁን ሃገራችን ዘመናትን ያስቆጠሩ በርከት ያሉ ችግሮች አሉባቸው። ችግሮቹን መንግስት ብቻውን ታግሎ ሊፈታቸው እንደማይችል አሣምረን ተረድተናል። ዛሬ የሁላችሁንም በር ለማንኳኳት ስንወስን ሃገር በዕውቀት እንጂ በልበ ብርሃንነት እንደማይመራ ተገንዝበን ነው። ሃገር በመገንባት ሂደት ውስጥ ህዝብ፣ መንግስት እና ባለሃብቶች ትልቅ ድርሻ አላቸው። ይሁን እንጂ ሁሉም በዕውቀትና በጥበብ ካልተሳሰሩና ካልተደጋገፋ ወንዝ መሻገር አይችሉም።

ምሁራን ያለችውን እውቀት ወደ ተጨባጭ ጠቀሜታ መቀየር የሚችሉት ብቻቸውን በመጓዝ አይደለም። ከመንግስት ጋር አብሮ መሥራትም ፖለቲከኛነት አይደለም። ይልቁንም ዕውቀትን ወደ ህዝብ ለማድረስ ዋነኛ ድልድይ ከሆነው አካል ጋር አብሮ መስራት ነው። የፖለቲካ ሣይንስ ምሁራን እንደሚናገሩትም የአንፃራዊነት ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከፖለቲካ ፈፅሞ ነፃ የሆነ ሰው የለም።

ስለሆነም ተገቢነት የሌለውን የፖለቲካ ሃሜት በመፍራት ወይም ይህንኑ ሰበብ በማድረግ መራራቅ ለማናችንም አይበጀንም። ተራርቀን አይተነዋል፤ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ገድል መፈፀም የሚያስችል እውቀትና ችሎታ እያለን “የጋን መብራት” ከመባል አላለፍንም። መለያየት፣ ፊት መዟዟር፣ በአለፈው ታሪካችን መወቃቀስም ሆነ የይስሙላ መቀራረብ ይብቃን።

የአማራ ህዝብ ችግር የሚፈታው ከልብ የመነጨ ፍቅር፣ አንድነት፣ እውነተኛ እህትማማችነትና ወንድማማችነት በመካከላችን ሲገነባ ነው። አማራ ክልል ፀጋው ያልተጓደለበት፣ ሁሉም ዘርፍ እንስራ ብንል ልማትን ለማምጣትና ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ወሳኝ የሚባል የሃብት መሠረት ያለው ክልል ነው። በእስካሁኑ ጉዟችን በገባን ልክ ህዝቡን ከድህነት ለማላቀቅ ያቅማችንን ተፍጨርጭረናል። ያም ሆኖ ያስመዘገብነው ውጤት ህዝባችን ሙሉ በሙሉ ከችግር ያላቀቀ አይደለም። የምናደርገው ሩጫ ብልሃት ቢጨመርበት፣ በዕውቀት ቢደገፍ ድህነት ከክልላችንና ከሃገራችን የሚቆይበት እድሜ በብዙ እጥፍ ሊያጥር ይቻል እንደነበር አሣምረን እንገነዘባለን።

የምናደርግላችሁ ጥሪ የይስሙላ አይደለም፣ ታሪካዊ ግዴታችሁ የሆነውን ይህን የአብረን እንስራ የጥሪ ደወል ሠምታችሁ በአንድነት በመሠባሰብና በተግባር አብሮ ለመራመድ ለቆረጣችሁ ምንጊዜም ከጐናችሁ በመሆን ለዚህ ተግባር የሚያስፈልገውን የመንግስት አገልግሎት በቀናነት ለመስጠት ዝግጁ ነን። ይህ አጋጣሚ ለእናንተ ግዴታ አይደለም። ይልቁንም ለረጅም ጊዜ ስትመኙት የነበረ ዕድል እንደሆነ አውቃለሁ። ዕድሉን መስጠት እና ሁኔታውን ማመቻቸት የመንግስት ድርሻ ቢሆንም መጠቀም ግን የእናንተ ብቻ ነው። ለመተባበርም ታሪክ ለመቀየርም እኔና እናንተ ከማንም አናንስም። ሳናጣ የጐደለብን፣ ሣይነጥፍ የደረቀብን፣ እያለን እንደሌለን የምንቆጠር ደካሞች አይደለንም።

እኛ የጠፋውን የማልማት፣ የጐበጠውን የማቃናት፣ የተቋጠረውን የመፍታት፣ የተወሳሰበውን መልክ የማስያዝ ብቃትና ተሠጥኦ ያለን ልዩ ልጆች ነን። አንድ ሆነን በመስራት ከእኛ አልፈን ለሃገርም የሚበቃ ትሩፋት መፍጠር እንችላለን። እነሆ መንገዱ ተከፍቷል፣ የጥላቻ መጋረጃውም ተቀዷልና በመሃሉ በመመላለስ ቤታችንን ቤት እናድርገው።

በድጋሜ አክብራችሁን ስለተገኛችሁ እያመሰገንኩ በዚህ አጋጣሚ ይህ ታሪካዊ የምሁራን መማክርት ጉባዔ እንዲቋቋም ምሁራን ለክልሉ ህዝብ ዕድገት የቻሉትን ሁሉ እንዲሰሩ በሚያዚያ ወር በዚሁ በባህር ዳር ከተማ ተገናኝተው ታሪካዊ መሠረት ድንጋይ ያስቀመጡ ምሁራንና በዚሁ ጉባዔ በተላለፈው ውሣኔ መሠረት የመማክርት ጉባዔ ለማዘጋጀት አስፈላጊ የሆኑ መነሻ ጽሁፍ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ እና ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት ትክክለኛ የሆነውን የምሁራን ትጋት በአሣዩን እና የአንድነት ተምሣሌት በመሆን ሌት ተቀን ለሰሩ የኮሚቴ አባላት ያለኝን ምስጋና ለማቅረብ ቃላት የለኝም። በተጨማሪም ከዚህ መማክርት ጉባኤ መክፈቻ ቀን ቀደም ብሎ በሙያቸው በመደራጀት የክልሉን የግብርና ልማት ዘርፍ ለማገዝ ሥራ ለጀመሩ የግብርና ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች ላሳዩት ቁርጠኝነት ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ።

አመሰግናለሁ!!!
ምንጭ፦ የአቶ ንጉሱ ጥላሁን ፌስቡክ ገፅ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: andm, gedu, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule