• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመጥበብ ቅድሚያ ለ “እምዬ ኢትዮጵያ”

September 16, 2012 02:01 pm by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል በወገኖቹ የሚፈቀር፣ የሚከበርና አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ የሚደረግለት የህዝብና የአገር አለኝታ ነው። ክቡር ህይወታቸውን ሳይሳሱ ላገራቸው ሲሉ አሳልፈው የሚሰጡትን ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የምናከብራቸውና ልንከባከባቸው የሚገባው ልክ ያይናችን ብሌን ያህል ነው። “ክቡር ለውድ ኢትዮጵያዊ ሰማዕታት” ሲባል እንዲሁ መፈክር ለማለት ሳይሆን ከልባችን፣ ከውስጣችን፣ የመስዋዕትነታቸውን ክብር ከቶውንም ልንዘነጋው የሚቻለን ባለመሆኑ ነው። ሌላ ምክንያት የለውም። በቃ!!

የምንኮራበት መከላከያ እንዲኖረን አጥብቀን ስለምንመኝ ያገር ኩራት የሆነው መከላከያችን በክልል፣ በዞንና በጎጥ አንሶና የተዋረደ ስብዕና ተላብሶ እንዲዋቀር ኢትዮጵያውያን አይፈቅዱም። አገራችን ከምትገኝበት የጂኦ ፖለቲካል አቀማመጥ አንጻር ብሄራዊ ስብዕና ያለው፣ ህዝብንና አገርን የሚያስቀድም የመከላከያ ኃይል ሊኖረን ይገባልና፡፡ በጎጥና በዘር ፖለቲካ የተተበተበ አመለካከት ያላቸው ክፍሎች በመከላከያ ሃይላችን እንዲቀልዱበት አንፈቅድም። ክብሩንና ሞገሱን አመናምነው ወገኑን የሚወጋና የሚያፍን የማፍያ ይዘት እንዲኖረው አንፈልግም። የእስካሁኑ ይበቃል!!

ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአገሪቱን መከላከያ እንደ ጠላት በመቁጠር በታትኖ መሳቂያ አድርጎናል። አየር ኃይላችንና ባህር ኃይላችንን አፍርሶ የወጠጤዎች መጫወቻ አድርጎናል። በዚህ አሳፋሪ ታሪክ አገር አፍሯል። ተዋርዷል። ንጹሃን ትርጉም በሌለው ጦርነት ተማግደዋል። ለአገር ሲዋደቁ የነበሩ ወገኖች እንደጠላት ታይተው እንደ እቃ መጣላቸው ለታሪክ የሚተው አቶ መለስ የፈጸሙት ታሪካዊ ግፍ እንዳለ ሆኖ፣ በባድሜ ወረራ ወቅት አቶ መለስ ያደራጁት የልምድ ጦርና አመራሩ ፍጥረቱ የተበላሸ በመሆኑ ወረራውን መመከት ሲያቅተው በዳግም ጥሪ አገሩን የታደገው ይኸው ወንጀለኛ ተደርጎና “የደርግ ሠራዊት” ተብሎ የተጣለው ወገን ነበር።

ብሄር፣ ክልል፣ ቀበሌ፣ ዘርና ቂም ሳያግደው በፈንጂ ላይ እየተረማመደ አገሩን ነጻ ያወጣ ወገን ዛሬም አይታመንም። ከደጀን ድጋፉን ሰጥቶ ለድል ያበቃ ህዝብ አሁንም ለለቅሶ እንጂ ለሃላፊነት አይታጭም። ከልምድና ከውድቀት መማር የማይችለው ኢህአዴግ ይህንን ህዝብና ወገን ማስቀየሙን ገፍቶበታል። የሰሞኑ ሹመትም የሚያጠናክረው ይህንኑ ነው። ያሳፍራል። ያሳዝናል።

በቅርቡ ኢህአዴግ ሹመት የሰጣቸው ጄኔራሎች ስልጣን የተቀበሉበት አግባብ ትክክል ሆኖ አላገኘነውም። ይህን መሰል ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመት የሚቀርበው በአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሲገባው ይህ አልተደረገም። ከሁሉም በላይ ደግሞ የተሰጠው ሹመት የአንድ ብሔር (የትግራይ) አባላት የተካተቱበት፣ ፍጹም ወገንተኛ፣ ሌሎች የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች ያገለለ፣ የኢትዮጵያ ኩራትና መመኪያ የሆነውን የመከላከያ ሃይል የሚያሳንስ ሆኖ ይሰማናል።

ታላቁን የመከላከያ ሃይል በማሳነስ ከህዝብና ከአባላቱ አመኔታ የሌለው ማድረግ ዞሮ የሚጎዳው ኢህአዴግን ሳይሆን አገራችንን ነው። የመከላከያ ሃይላችን ፍጹም ህዝባዊ፣ ሚዛናዊ፣ ሁሉን አቀፍ፣ ሁሉም ባለቤት በሆነበት ደረጃ ባስቸኳይ ሊደራጅ ይገባል። አቶ መለስ የመተማመን ፖለቲካ በመዘርጋት ዜጎችን ወደ አንድ አመለካት ማሰባሰብ ሲገባቸው ብቻቸውን ለመምራት ካላቸው የኖረ ህልም ተነስተው አገሪቱን ተቋም አልባ በማድረግ የተወሳሰበ ችግር አውርሰውን እሳቸው አርፈዋል። የተቀሩት ከመለስ የስህተት ጎዳና በመውጣት የማስተካከያ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ “በተጀመረው ይቀጥላል” በሚል መዝሙር እያደነቆሩን ነው። ይባስ ብለው የፖለቲካውን ክፍተት ለመሙላት ህወሃት ወታደራዊና የደህንነት ተቋሞቹን እያጠናከራቸው ነው። የራሱን ሰዎች ይሾማል። የራሱን ሰዎች ያስታጥቃል። የራሱን ሰዎች በኢኮኖሚ ያበለጽጋል። የራሱን ሰዎች ከፍ ከፍ ያደርጋል። የራሱን ሰዎች ታማኝ አድርጎ አብዛኞችን ይገፋል። አሁንም እስከመቼ በዚህ መልክ ይቀጥላል?

አቋማችን አንድ ነው። ህወሃት ከብሄራዊ ክብርና ሞገስ ይልቅ ጎጥና ጎሳ ብሶበት የሚርመጠመጥበት አካሄድ ማንንም ተጠቃሚ አያደርግምና ያቁም! አገሪቱን ወደ ወታደራዊ አመራር ለመውስድ የሚያደርገውን ሩጫ ይግታ! ድርጊቱን ኢትዮጵያውያን ሁሉ በህብረት ይቃወሙት! የሁሉም ስህተቶችና የመጥበብ በሽታዎች ዞሮ የሚጎዳው አገራችንን ነውና ቅድሚያ እምዬ ኢትዮጵያን ብቻ!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yonas says

    September 17, 2012 07:20 am at 7:20 am

    Guys, keep up the good work !

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule