• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትንሽ ምስክርነት ስለ መረራ ጉዲና (ዶ/ር)

January 7, 2015 06:06 pm by Editor 2 Comments

ከመሰንበቻዉ መረራ ጉዲና ከ25 ዓመታት በላይ ካስተማረበት ዩኒቨርሲቲ ተባረረ የሚለዉ አስገራሚና አስደንጋጭ ወሬ ከተዛመተ በኋላ አነጋጋሪነቱ ሞቅ ብሏል፡፡ (በጨዋታችን ላይ የማከብረዉ መምህሬ ስለሆነ አንተ እያልኩ ነዉ የምጠራዉ … እሱም ቢሆን አንቱታዉን ብዙም የሚፈለገዉ አይደለም … አዉቃለሁ)፡፡ በይፋ ከዩኒቨርሲቲዉ መሰናበቱን የሚያስረዳ ደብዳቤ እንደረሰዉ ባይገልጥም ነገሩ እሳት ካየዉ … ነዉ እና የምናዝን እናዝናለን፡፡

ዶ/ር መረራን ሳዉቀዉ

ለመጀመሪያ ጊዜ መረራ የሚባል ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ … በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዉስጥ ጎልቶ መዉጣት የጀመረዉ ይመስለኛል በ1992 ብሔራዊ ምርጫ ወቅት ነዉ፡፡ በዚያን ጊዜ የደመቀ ባይሆንም ጥቂት ፖለቲከኞች ገዢዉን ፓርቲ ሲሞገቱ የሚያሳይ የቅድመ ምርጫ ክርክር በቴሌቪዥን ይለቀለቅ ነበር፡፡ ያኔ ታድያ የብዙዎችን ቀልብ የሳበዉ በእኩልነት የምንኖርባትን አዲሲቱን ኢትዮጵያን በጋራ እንመስርት የሚል ጎልቶ የሚሰማ የአንድ የፖለቲካ ሳይንስ ምሑር ድምፅ ነበር፡፡ … ለእኩልነት፣ ለጋራ መብት መከበር፣ ለመቻቻል፣ ለጋራ ብልፅግና፣ ለሰላም፣ ለመጪዉ ትዉልድ አስበን በጋራ እንስራ የሚለዉ ጥሪዉን ሲያስተላልፍ ይታወሰኛል፡፡ በተለይ ሰማያዊ ቀለም ያለዉ ሙሉ ጅንስ አለባበሱን አረሳዉም፡፡ በጋራ እንስራና እንተባበር በሚለዉ የዘወትር ጥሪዎቹ ይህ ፖለቲከኛ አሁንም በኢትዮጵያ ታሪክ ዉስጥ በጉልህ ታሪኩን መፃፍ ቀጥሏል፡፡

በቴሌቪዥን መስኮት የማዉቀዉን ሰዉ ለመጀመርያ ጊዜ በአካል ያገኘሁት 1995 የሁለተኛ ዓመት የዩኒቨርስቲ ትምህርቴን ለመቀጠል በፖለቲካል ሳይንስና ኢንተርናሽናል ሬሌሽንስ ዲፓርትመንት በገባሁበት ወቅት ነበር፡፡ በወቅቱ ፖለቲካል ገቨርናንስ የሚል የትምህርት ያስተምረን ነበር፡፡ አስታዉሳለሁ በርካቶቻችን ክፈለ-ጊዜዉን በናፍቆትና በጉጉት እንከታተል እንደነበር፡፡ ዶ/ር መረራ በሌሎች መድረኮች ላይ እንደሚያሳየዉ ተጨዋችነትና አዝናኝነት በክፍል ዉስጥም ኮሚክ ነገሮችን ይናገራል፡፡ በዚህ ዘዴዉ ትምህርቶቹን ተወዳጅ ከማደረጉም በላይ በቀላሉ ለመረዳትና ከነባራዊ ሁነቶች ጋር ለማገናዘብ እንዲቻል አድርጎ የማስተማር ብቃት እዳለዉ ብዙዎቻችን እንመሰክርለታለን፡፡ ከሁሉ የማረሳዉ በየንግግሮቹ መጨረሻ ላይ “Generally” የሚለዉን ሲሆን ሁሉ ነገር ጀነራሊ ከሆነ እንዴት ነዉ ነገሩ ብለን ብንጠይቀዉ እየሳቀ ልምድ እንደሆነበትና እየሳቀ አባባሉን ከቁም ነገር እንዳይወሰድ ያሳስበን ነበር፡፡

ዶ/ር መረራን በክፍል ዉስጥና ከክፍል ዉጪ ስናዉቀዉ የተለየ ሰዉ ነዉ፡፡ በሌላ አነጋገር በክፍል ዉስጥ ሲያስተመር ፍፁም ሊባል በሚችል ሁናቴ ሚዛናዊና ገለልተኛ አቛሞችን ነዉ የሚያንፀባርቀዉ፡፡ የፖለቲካ እምነቱን እና አመለካከቱን በግድ ልጋታችሁ የሚል ስብእና እንደሌለዉ ወዳጆቹ ብቻ ሳንሆን ኢህዴጋዊ አቛማቸዉን በይፋ የገለጡ ተማሪ ጓደኞቻችን ጭምር ነበሩ የሚመሰክሩለት፡፡ የሚገርመዉ በ1997 የምርጫ ዋዜማ እንኳን ነገሮች ተሟሙቀዉ በተለይ ዶ/ር መረራ ሕብረት የሚባለዉን ጥምር ፓርቲ እየመራ ከቅንጅት ጋር ኢሕዴግን እንደዚያ ሲያንጰረጵረዉ፤ ዉጪ ባለዉ አቋሙ እያወቅነዉ ክፍል ዉስጥ በጉዳዩ ላይ አሰተያየት ለመስጠት እኳንን አለመፈለጉ (ብዙዎቻችን ወቅታዊ ፖለቲካዉን የተመለከቱ ጥያቄዎች እናነሳለት ነበር) የቱን ያህል ሞያዉን የሚያከበርና በአካዳሚክ ነፃነት የሚያምን መሆኑን ለማሳየቱ እንመሰክር ነበር፡፡

ከ1997 ምርጫ ግርግር በኋላ ለድህረ ምረቃ ትምህርት ተመልሼ ሳገኘዉም በቅንነት ከማስተማር በቀር በክፍል ዉስጥ ፓርቲያዊ የሆኑ ነገሮችን ላለማንሳት ሲጠነቀቅ አዉቀዋለሁ፡፡ ዶ/ር መረራ ቢሮዉ ለሁሉም ተማሪዎች ከፍት የሆነ ሲሆን ማንኛዉንም ጉዳይ ይዞ ሄዶ ምክር ለመጠየቅ የሚመችና ቤተሰባዊ መንፍስ ያለዉ ሰዉ ነዉ፡፡ ከሌሎች የዲፓርትመንቱ መምህራን በተለየ መልኩ ቢሮ ዉስጥ ሲቀመጥ በሩን አይዘጋም፡፡ ስለሆነም ማንም ሰዉ ቢሄድ በቀላሉ ሊያገኘዉና ሊያወየዉ እንደሚችል አዉቃለሁ፡፡ በአጠቃለይ እንደ አብዛኞቹ የቀድሞ የዩኒቨርሲቲዉ መምህራን ፊዉዳላዊ አመለካከት የሌለዉ ሰዉን በመተባበር የሚያምን ሰዉ ነዉ፡፡

ከእዉቀት አንፃር ካየነዉ በፍጹም የሚታማም አይደለም፡፡ ከብዙዎቹ የላቀ ሁለገብ የሆነ ችሎታና እወቀት ያለዉ ሰዉ ነዉ፡፡ ሲያስተምር፣ የጥናት ፁፎችን ሲያማክር፣ ሞያዊ አስተያየቶችን ሲሰጥ፣ እንዲሁም በተለያዩ መድረኮች ንግግር ሲያደርግ አፍ የሚያሰከፍት አይነት ነዉ፡፡ የትምህርት ክፍሉ አሉት ከሚባሉ የጠለቀ እዉቀትና የማስተማር ችሎታ ካለቸዉ የአንድ እጅ ጣት የማይሞሉ መምሀራን ግንባር ቀደሙ ነዉ ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡

ማን ይጎዳል?

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በብዙ መለኪያዎች ከነበረዉ ዝና፣ ክብርና ማእረግ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወረደ መምታት ብቻ ሳይሆን እየዘቀጠ እደሆነ ይነገራል፡፡ ይህ ጉዳይ የሚታየዉ ከአጠቃለዩ ሃገራዊ የትምህርት ጥራት መጓደልና የደረጃ ማሽቆልቆል ጋር ብቻ መሆን የለበትም፡፡ ይልቁንም የዩኒቨርሲቲዉ ዛሬ ባለበት ደረጃ ላይ መገኘት እንደ አንድ ቀደምት ሃገራዊ ተቋም መፈራረስና ሁለነተናዊ ዉድቀት ነዉ፡፡ ያን የመሰለ ታሪካዊና በርካታ ምሁራንን ለሃገሪቱ ያፈራ ተቋም ዛሬ ላይ በአለም ከፍተኛ ዝና ካላቸዉ የትመህርት ተቋማት ጋር መወዳደር ሲገባዉ በአፍሪካ ዉስጥ ካሉት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነፃፀር እዚህ ግባ የሚባል ቦታ የለዉም፡፡ ይኼ ጉዳይ በዩኒቨርሲቲዉ ዉስጥ ላለፍን ሁሉ አንግት የሚስደፋ ጉዳይ ሆኖ ይገኛል፡፡ ለምን ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ብራንድ አይኖራትም ብለን ለምንጠይቅ ምላሹ ምን ይሆን?

ከዩኒቨርሲቲዉ ዝቅ ብለን የፖለቲካ ሳይንስ እና ኢንተርናሽናል ሬለሺንስ (PSIR) የሚባለዉን የትምህርት ክፍል ያየን እንደሆነ የበለጠ የሚስደነግጥ ማሽቆልቆል ሂደት ዉስጥ እንዳለ ለመረዳት አያዳግትም፡፡ በርካታ እጋፋና ወጣት መምህራኖች በየጊዜዉ እየለቀቁ በመዉጣታቸዉ የትምህርት ክፍሉ በህንድ መምህራን እና አንዳንድ ነዉረኛ ሰዎች እንዲሞላ ተድረጓል፡፡ እዚህ ላይ የማስታዉሰዉ ከጥቂት ዓመታት በፊት የወቅቱ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዘዳንት የነበሩት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ዘመድ እንደሆነ በፉከራ ይናገር የነበር ዶ/ር ኤርሚያስ አበበ (ያባቱን ስም ካሳትኩ ይቅርታ) የሚባል ሰዉ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎችን ‘Foreign Policy and Diplomacy’ የሚል የትምህርት አይነት እንዲያስተምር ተመድቦ በርካታ የሚያሳፍሩ ተግባሮችን ሲፈፅም እንደነበር ምስክርነት ለመስጠት እችላለሁ፡፡ በስካር ጥንብዝ ብሎ በወሳንሳ በመጠጥ ቤት ጓደኞቹ ተደግፎ ከመምጣቱ በተጨማሪ በነዉረኛ ስድቦች ተማሪዎችን ይዘለፍ ነበር፡፡ የትምህርት ክፍሉ አሉት የሚባሉ ማምህራን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ እንኳን ፍልሰት በሚመስል መልኩ በመልቀቃቸዉ የቱን ያህል የተዳከመ መሆኑን መገመት አያዳግትም፡፡

እናም የዶ/ር መረራና መሰል አንጋፋና ጠንካራ አመለካከት ያላቸዉ ምሁራን መልቀቅ የትምህርት ክፍሉን እና ዩኒቨርሲቲዉን ብቻ ሳይሆን በመላ ሃገሪቱ ላይ ሊደርስ የሚችለዉን ኪሳራ ማስላት አዳጋች አይሆንም፡፡

topha07@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. pape says

    January 10, 2015 09:55 am at 9:55 am

    don’t worry, there are so many educated peoples! We ethiopians are rech in. . .

    Reply
  2. Eugene-man says

    February 6, 2015 09:38 pm at 9:38 pm

    Ethiopia affected more than him. cz his gentility gives better work for him on else World. long live for our hero!.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule