• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሟቹ ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም የተሰበሰበው ገንዘብ ያስከተለው እሰጥ አገባ

November 4, 2018 07:30 am by Editor Leave a Comment

“በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም በጎፈንድሚ የተሰበሰበውን 73 ሺህ 9 መቶ ዶላር ወደ አካውንት ለማስገባት ፈቃደኛ አይደለሁም። ምክኒያቱም በኮሚቴው እምነት የለኝም” አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ።

“በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም በጎ ፈንድሚም ሆነ በማናቸውም መልኩ የተሰበሰበው ገንዘብ በስሙ ወደተከፈተው የባንክ አካውንት መግባት አለበት” የአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የህክምና ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ።

ይህ እሰጣ አገባ የተካሄደው ቅዳሜ ጥቅምት 24 በአፍሮዳይት ሆቴል የአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም የህክምና ገቢ ለማሰባሰብ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ኮሚቴ በጠራው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

ኮሚቴው ለሁለት የተከፈለበትን ጉዳይ አንስቶ ባቀረበው ሪፖርት ላይ እንደገለጸው በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም የተሰበሰበው ገንዘብ ጉዳይን አስመልክቶ የተጓዘባቸውን ርቀቶች ዘግቧል። ከአርቲስት ፍቃዱ የህክምና ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ አማካኝነት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው አካውንት ላይ በአሁኑ ወቅት 1,200,895.69 (አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ ስምንት መቶ ከስልሳ ዘጠኝ ሳንቲም) ብር እንደሚገኝ ገልጸው ቀሪውን በጎፈንድሚ የተሰበሰበውን 73,900 ዶላር ወደ አካውንት እንዲያስገባ ለቴድሮስ ተሾመ ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም ለመቀበል እንዳልቻለና በኮሚቴው አባላት ላይ እምነት የለኝም በማለቱ ልዩነት እንደተፈጠረ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ጥቅምት 23 ቀን 2011 ዓ.ም በጊዮን ሆቴል ተሰብስቦ የወሰነውን ቃለ ጉባኤ በንባብ አስደምጧል። ይህንን አስመልክቶም ምላሽ የሰጠው አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ “ህዝብ ገንዘቡን የሰጠኝ የእኔን ስም አይቶ ነው። በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም የተሰበሰበውን ገንዘብ በኮሚቴው የክራይሲስ ማኔጅመንት ችግር ምክንያት እምነት ስለሌለኝ ገንዘቡን ወደ ተባለው አካውንት ገንዘቡን አላስገባሁም። ወደፊትም በዚህ ገንዘብ ላይ ሙሉ ኃላፊነቱን የምወስደውም ሆነ እየወስድኩ ያለሁት እኔ ነኝ። ጠበቃዬም ገንዘቡን ገቢ እንዳላደርግ አማክሮኛል። ለዚህም ለህሊናዬም ሆነ ለፈጣሪ ታማኝ በመሆን ገንዘቡን ህጋዊ ወራሽ ይሆናሉ ብዬ ለማስባቸው ቤተሰቦቹ ጥቅምና ለሀውልቱ ማሰሪያ እንዲሆን እየተንቀሳቀስን ነው” ብሏል።

ሌሎች የኮሚቴ አባላት ደግሞ በአጠቃላይ የተሰበሰበውን ገንዘብ ወደ አንድ ቋት እንዲገባና ፍርድ ቤት የሚያሳውቃቸውን ህጋዊ ወራሾች መጠበቅ አለበት የሚል አቋም ይዘዋል።

ለአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም ከህዝብ የተሰበሰበው ገንዘብ መጨረሻ ምን ይሆን? አሁንም ምላሽ የለውም። በአርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ስም በተሰበሰበው ገንዘብ ላይ የተነሳው ንትርክ ከዚህ በኋም የጤና እክል ለሚያገጥማቸው የኪነጥበብ ባለሙያዎች ህዝብ በአግባቡ እንዳያግዝ የራሱን አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳያሳርፍ ስጋት አጭሯል።

(ዘገባ፤ ጴጥሮስ አሸናፊ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule