• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምነው ደም ደም አይለን?

June 8, 2018 05:11 am by Editor 1 Comment

ፍትህ ሳያደርቀው የፈሰሰን ፍዳ፣
ንስሀ ሳያጥበው የቆሸሸን ጓዳ፣
ዱለትን መቋደስ ከገዳዮች ጋራ፣
የሐጥያትም ሐጥያት የታሪክም ዕዳ!

ፍትህ ነፃነትን መብትን ተርበው፣
ኢፍታዊነትን እንደ አውሬ ተናንቀው፣
ስንቶቹ ተሰው ባሩድ ተመግበው?

ነፃነት ወይም ሞት በቃ ዘራፍ ብለው፣
ስንቶች ተሰውልን ጫካ ዱር ሸፍተው?

በእሬቻ በጥምቀት በመስጊድ ሰገዳው፣
በሰፈር መንደሩ በገጠር ከተማው፣
እንደ ፋሲካ በግ የታረደ ስንት ነው?

ባዶ ስድስት ጉድጓድ በጪስ የታፈነው፣
ቃሊቲ ዓለም በቃኝ የተዘቀዘቀው፣
ቅሊንጦና ዝዋይ በእሳት የነደደው፣
ሽሮሜዳ ታስሮ ጥፍሩ የወለቀው፣
ብር ሸለቆ አዘዞ ጉረኖ የገባው፣
ማሰቃያ ቦታው ጭራሽ ያልታወቀው፣
ስንት መከረኛ ምን ያህል ዜጋ ነው?

የጋንቤላን ምድር ሽፍን ያደረገው፣
ኦጋዴን በርሃን በጎርፍ የጠረገው፣
ምን ያህል ሬሳ ስንት በርሜል ደም ነው?

ጎንደር ደብረታቦር በባሩድ ያለቀው፣
ባህርዳር ወልድያ ስናይፐር የፈጀው፣
አምቦ ደብረ ዘይት ጥይት ያረገፈው፣
መች ተቆጥሮ ያልቃል ቆጣሪ ቢኖረው?

በሽሽት በስደት በአውሬ የተበላው፣
ባህርን ሲሻገር ድንብልዝ ያሰመጠው፣
ምን ያህል ኮረዳ ምን ያህል ጎበዝ ነው?

ወልቃይት ራያ ዘሩ የመከነው፣
በደኖ በገደል የተወረወረው፣
አሶሳ መተከል የተቆራረጠው፣
ከፋ ኢሉባቦር ሜጫ የከተፈው፣
አይምሯችን ያስላ ምን ያህል ሕዝብ ነው?

ይኸ ግፍ ሲፈጠም ለካስ ያለቀስነው፣
እርሾና አብሲት ጥለን በትኩስ ደማቸው፣
በተሰውት አጥንት ዳቦ ልንጋግር ነው፡፡

ጅቦቹ ሰው በሉ ስንል የነበረው፣
ለካስ የውሻ ጠጉር ካባ ደርበን ነው፣
ትርፍራፊ ልፋጭ መጎተት አምሮን ነው፡፡

በየ አደባባዩ ስንጮህ የነበርነው፣
ለካስ በሙታን ደም ገንፎ ልንሰራ ነው፡፡

አይ ጊዜ ፈታኙ አይ ጊዜ መስካሪው፣
ስንቱን አጭበርባሪ ከርሳም አጋለጥከው፡፡

በእርቅና በሰላም እያመካኘ፣
ስንቱ ይሁዳ ሰው ለሰይጣን ሰገደ፡፡

ዓለም ፍርደ-ገምድል ዓለም ወለወልዳ፣
ቀጣፊን አጽዳቂ ሐቀኛን ኮንና፡፡

በእርቅና በሰላም ስንት ሆዳም ነገደ፣
የሰማእት እሬሳ እየተራመደ፡፡

የሰማእት ሥጋ ቅርጫ ለመቃረጥ፣
በሙታንም አጥንት ንግድ ቤት ለመክፈት፣
ከገዳዮች ጋራ አብረን ስንዶልት፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ገዳይ ችሎት ሳይቀርብ ሟችም ሳያገኝ ፍርድ፣
ፍትህ ገደል ገብታ ንስሃ እንጦሮጦስ፣
እርምን ልንጠሸቅም ከገዳይ ስንቀርብ ማድ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይሰቀጥጥ?

ሥጋውን እንጀራ ደሙንም ሰርተን ወጥ፣
እየሸመለልን ሰማእት ልንውጥ፣
ከነፍሰ በላዎች አብረን ስንቀመጥ፣
ምነው ደም ደም አይለን? ምነው አይለን ስቅጥጥ?

ይገርማል! ሰው ከንቱ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)

ሰኔ ሁለት ሺ አስር ዓ.ም.

 

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. እውነቱ ይነገር says

    June 18, 2018 05:05 pm at 5:05 pm

    ወገኔ አቶ በላይነህ

    I would like to say thank you for your message. Please keep it up!

    ጥያቄ አለኝ???

    እውነተኛና ግልጽ መልስ ያለው ሰው በመረጃ አስደግፎ ይመልስልኝ!

    1)የኢትዮጵያውያን ዓይኖች መቼ ነው እንባቸው የሚደርቀው/የሚታበሰው?

    2)እየተባባሰ ለመጣው ለኢትዮጵያውያን የዘመናት እንባ ምክንያቱ/ምንጩ በእውነት ምንድነው?

    3)የውጭ ሃገር ወራሪ ጠላት ያላስለቀሰን እኛ ኢትዮጵያውያንን ለምንድነው የራሳችን ወገኖች የደም እንባ እንድናነባ የሚያደርጉን????

    4)አማራው በእውነት በተናጠል ኢትዮጵያንን በሙሉ በማን አለብኝነት ረግጦ በገፍ ገዝቷልን????

    5)በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በእውነት አንዱ ብሔረ ሰብ በሌላው ብሔረ ሰብ ሆነ ብሎ በደል ሠርቷል ወይስ እንደ ማንኛውም ሃገር የሕብረተሰብ እድገት-ታሪክ ሃይልና ጉልበት ያገኘው ጎሳና ሰፈርተኛ በነበረው ንቃተ ህሊና ላይ ተመስርቶ በሚፈጠር ግጭት የመጣ ማንነት ላይ የተመሰረተ ታሪክ?

    6)የሸዋ መሳፍንት ታሪክ ሲጠና ስንቱ አማራ ስንቱ ደግሞ ኦሮሞ እንደነበረ እስቲ በዳታ አስረዱኝ???

    7)በሃይለ ስላሴ፣ በደርግና በወያኔ መንግሥት ዘመናት ወቅት አመራር ላይ የነበረውን አካል በብሔረሰብ ደረጃ በመረጃ አስደግፋችሁ/አሁን ዛመኑ የመረጃ ጊዜ ስለሆነና በአሉባልታና በወሬ ወለደ ወሬ ይህን ትውልድ ማታለል ስለማይቻል/ እስቲ ንገሩን???

    ሁሉም የዘራውን ስለሚያጭድ እንጠንቀቅ?
    ወንድምን ከወንድሙ ጋር ማጋጨቱ ይብቃ?
    እውነት ነጻ ያወጣልና በጋራ
    ለእውነተኛ የጋራ ሃገርና
    መልካም ሥራ በእውነት እንነሳ?

    ወስብሐት ለእግዚአብሔር
    ሕዝባችንን ማስተዋል ይስጥልን!
    አሜን።

    እውነቱ ይነገር
    ከለሁበት

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule