• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ችጋርና የእውቀት ችጋር

November 30, 2015 10:02 am by Editor Leave a Comment

በፈረንጆች ባህል እውቀት ሥልጣን ነው፤ እንዲያውም እውቀት ኃይል ነው ይላሉ፡፡ በኢትዮጵያ ባህል እውቀት ሥልጣን የለውም፤ እንዲያውም ሥልጣን እውቀት ይመስለናል፡፡

በ1951 ዓ.ም. በትግራይ ችጋርን በዓይኔ አይቻለሁ፤ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፤ በአካሌ ቀምሼዋለሁ፤ ጠኔ ይዞኝ ተደግፌ ወደቤቴ ገብቻለሁ፡፡ በመቀሌ ያየኋት አንዲት የመቀሌ ወጣት እናት ከነሕጻንዋ በአእምሮዬ ተቀርጸውና ተቆራኝተውኝ በሕልሜም በእውኔም እየወተወቱኝ ስለችጋር እንዳጠና አስገደዱኝ፡፡

ችጋርን እያገላበጥሁ ከሰባት ዓመታት በላይ አጠናሁ፤ የጥናቴ ውጤት RURAL VULNERABILITY TO FAMINE IN ETHIOPIA: 1958-1977 በሚል ርእስ በህንድ አገር፣ በኒው ዴልሂ ከተማ ታትሞ በ1977 ዓ.ም. (በአአ በ1984) ወጣ፤ በአሜሪካ የተማርሁበት ክላርክ ዩኒቨርሲቲ ለጥናቱ ድጎማ የሚሆን የ$30,000 ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በእኔ በኩል አበርክቶአል፤ ለእኔ የተረፈኝ አንድ መቶ መጻሕፍት ብቻ ነበር፡፡

እአአ ከ1984 ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ መጽሐፉ ይሸጣል፤ እኔ ሳልጠየቅ አንድ INTERMEDIATE TECHNOLOGY Publications (9 King Street, London WC2E 8HW,UK), የሚባል የእንግሊዝ ኩባንያ እአአ ከ1986 ጀምሮ በተደጋጋሚ እያሳተመ ይቸበችበዋል፤ ለእኔ አንድ ሣንቲም አልደረሰኝም! በዚህ የችጋር ምክንያት ሌሎች የደረሱብኝን ነገሮች መግለጹ አይደለም፤ ጥቁር ከመሆን፣ ኢትዮጵያዊ ከመሆን፣ … የተነሣ የተሰነዘሩ ነገሮች አሉ፡፡

ከዚያም በኋላ አንዳንድ ጥያቄዎችን ለመመለስ ስል በሰሜን ሸዋና በደቡብ ወሎ አውራጃዎች በጣም ዝርዝር የሆነ ጥናት በሁለት መቶ ሰማንያ አምስት መንደሮች ጥናት አካሂጄ ውጤቱ እአአ በ1991 SUFFERING UNDER GOD’S ENVIRONMENT: A Vertical Study of the Predicament of Peasants in North-Central Ethiopia, (Published by AFRICAN MOUNTAINS ASSOCIATION AND GEOGRAPHICA BERNENSIA, Marceline, Missour, USA, 1991) ታተመ፡፡


ዛሬ በቴሌቪዥን ስለድርቅ፣ ስለችጋር የሚያወሩና በተለያየ ቦታ የሚጽፉ ኢትዮጵያውያን እነዚህን ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን መጽሐፎች ሲሆን ሁለቱንም፣ አለዚያ አንዱን ያላነበቡ ከእግር ጥፍራቸው እስከራስ ጸጉራቸው በእፍረት ይከናነቡ፤ የኢትዮጵያ ታሪክም ሆነ ማኅበራዊ ሁኔታ በእውቀት፣ ማለትም በተጣራ እውቀት እየዳበረ ከትውልድ ወደትውልድ እንዳይተላለፍ የሚያደርገው ይህ አስመሳይነትና የመንፈስ ውርደትና የአእምሮ ስንፍና ነው፤ እውቀት የማኅበረሰብ ሞተር ሆኖ ወደፊት የሚያራምደው ከቀደመው ትውልድ የተረከቡትን በሚገባ አጥንተውና አዳብረው ለሚቀጥለው ትውልድ ሲያስረክቡ ነው፤ ወይም የተረከቡት የማይረባ መሆኑን አስመስክረው ሲጥሉትና በሌላ ሲተኩት ነው፡፡

ሰሞኑን የማየውና የምሰማው ያሳፍረኛል!

በዚህም ምክንያት ከትውልድ ወደትውልድ እውቀት ሆኖ የሚተላለፈው ከሥልጣን ጋር የተያያዘው ብቻ ነው፤ ሥልጣን፤ የእህል ምርት እጥረት፤ የእህል ምርት እጥረት የሚከሰተው ድርቅ የተፈጥሮ ቀውስ፣ ችጋር በጭቆና መኖር፣ ችጋር ማንን ያጠቃል?

ሰሞኑን ብዙ ጸሐፊዎች ስለችጋር ያወራሉ (አብዛኛዎቹ የሚሉት ረሀብ ነው)፤ እንደሚመስለኝ እነሱ መጻፍ ከመጀመራቸው በፊት ስለችጋር ማንም ያሰበ፣ ማንም የጻፈ አይመስላቸውም፤ ስለዚህም በነሱ ቤት የሚጀምሩት ከዜሮ ነው፤ ስለዚህም በረሀብና በችጋር መሀከል ያለውን ልዩነት አያውቁትም፤ ስለዚህም በድርቅና በችጋር መሀከል ያለውን ልዩነት አያውቁትም፤ ስለዚህም በችጋሮች መሀከል ያለውን ልዩነት አያውቁም፤ ሳያውቁ ለማሳወቅ መሞከር ከምን ይመጣል?

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

ኅዳር 2008


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule