• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አሳዛኙ የትውልድ ህይወት በሳውዲ አረቢያ «ጂዛን» ከተማ!

January 13, 2014 10:57 pm by Editor 1 Comment

ጂዛን እየተባለ በሚጠራ የሳውዲ አረቢያ ግዛት ውስጥ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌለውን ጨምሮ ከ50 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ይነገራል። የጂዛን ከተማ ሳውዲ አረቢያን ከየመን የሚያዋስን ከተማ እንደመሆኗ በባህር የሚመጡ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወደ ሪያድ እና ጅዳ ከተማ ለማቅናት በመሸጋገሪያነት እንደሚጠቀሙባት ይነገራል።

በዚች የድንበር ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጉዳዩ በወል በማይታወቅ ምክንያት ያለ ፍርድ ለ 4 እና 5 አመታት ታስረው የሚሰቃዩባት ከተማ መሆኗን የሚነገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ወደ ሃገር ለመመለስ ጥያቄ ያቀርቡ አያሌ ወገኖቻችንም በሪያድ የኢትዮጵያን ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስካሁንም ምላሽ ባለማግኘቱ ህይወታቸው አደጋ ውስጥ መሆኑን ይናገራሉ ። ይህ በዚህ እንዳለ ከሁሉም በላይ እስከፊ አስከፊ በለው የሚገልጹት ምንጮች ከሶስት አመት በፊት በደረሰባት ከባድ የመኪና አደጋ ከወገቧ በታች በድን «ፓራላይዘድ» እንደሆነች የሚነገርላት ኢትዮጵያዊት እህት በዚህ ከተማ ውስጥ በተለምዶ «ኦድ ደርብ » እይተባለ በሚጠራ አካባቢ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ላለፉት ሶስት አመታት የአልጋ ቁራኛ ሆና ሃገር እና ወገን አልባ ሆና ሆስፒታል ውስጥ ለመኖር መገደዷ የአብዛኛውን ወገን ልብ የነካ መሆኑን ምንጮች አክለው ይገልጻሉ ።

በተለይ ስለጉዳዩ በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት መረጃ እንዳላቸው የሚናገሩ ወገኖች የመንግስት ባለስልጣናቱ ዝምታን መምረጣቸው ለወገን ህይወት ደንታ የሌላቸው ሃላፊነት የጎደላቸው መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል። የተጠቀሰችው ኢትዮጵያዊት ወጣት በአካሏ ላይ ለደረሰው አስከፊ የመኪና አደጋ «ኢንሹራስ» ካሳ ሳታገኝ ይቅርታ እንዳደረገች ተድረጎ ሆስፒታል ውስጥ እንዳስፈረሞት የሚገልጹት ምንጮች ወጣቷ አደጋው ከደረሰባት ግዜ ጀምሮ ወደ ሃገር ለመግባት ያደረገችው ጥረት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ የመግንስት ዲፕሎማቶች ድጋፍ እና ትብብር ማጣት ለበለጠ ስቃይ መዳረጓን ገልጸዋል። ወጣቷ በቤት ሰራተኝነት ከ አራት አመት በፊት ወደ ሳውዲ አረቢያ እንደገባች የሚነገርላት ወጣት ከዲጃ መሓመድ ሑሴን ትውልድ እና እድገቷ በአማራ ብ\ክ\መ\የኦሮሚያ ማህበረሰብ ዞን “ደዌ” ከሚባል አካባቢ በመሆኑ ከአረብኛ እና ከኦሮምኛ ቋንቋ ውጭ መናገር እንደማትችል የሚገልጹት ምንጮች ወጣቷ በአሁኑ ግዜ በተፈጠረው አጋጣሚ ህይወቴ ሳታልፍ ከቤተሰቦቼ ጋር እንድገናኝ እርዱኝ እያለች ብትማጸንም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘች ይናገራሉ።

ይህ በዚህ አንድ ወጣት ካሊዶ ኣሕመድ የተባለ ኢትዮጵያዊ በተመሳሳይ አደጋ በጂዛን ጀነራል ሆስፒታል ያልጋ ቁራኛ ከሆነ ድፍን ሁለት ኣመት ከስድስት ወራት እንዳስቋጠረ የሚናገሩ ምንጮች ወጣቱ ፓራላይዝ ከመሆኑም በላይ አይናገርም፣ አይሰማም፣ አያይም። እጅና እግሩ ከብረት አልጋው ጋር ተያይዞ እንድሚገኝ ገልጸዋል ። ወጣቱ ለረጅም ግዜ በመተኛት በሚፈጠር የሰውነት መቆሳሰል የተነሳ ወጣቱ በተጨማሪ በህክምናው አነጋገር \በድ ሶርስ\ በተባለ መጎሳቆሉን ይናገራሉ። ወጣቱን ሳይንሳዊው ህክምና አሳስሮ ወይም በቁሙ ገንዞ እንዳሰቀመጠው የሚናገሩ እነዚሁ የአይን እማኞች የጂዛን ትራፊክ ፅ\ቤት በተደጋጋሚ ለጅዳ እና ሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ቢያሳውቁም እስካሁን ወጣቱን ማንም ያየው እንደሌለ ይናገራሉ ።

በቀርቡ ጅዳ እና በጂዛን ከተማ የሚኖሩ ከስደት ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እሮሮ አስመልክቶ በተከታታይ እየዘገበ በሚገኘው በጅዳ የጀርመን ራዲዮ ድምጽ «ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ» ዘገባ የተበሳጩ በጅዳ የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማቶች ጋዜጠኛውን ህገወጥ በሆነ መንገድ ወገኑንን በነጻ ለማገልገል በጸሃፊነት ተመርጦ ሲሰራ ከነበረበት ወገን ለወገን ከሚል አንድ ግዜያዊ ኮሚቴ ማገዳቸው የሚታወስ ነው።

Ethiopian Hagere ከጅዳ በዋዲ ብፌስቡክ በኩል ለጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ephrem Alemayhu says

    April 24, 2014 10:49 pm at 10:49 pm

    ykfet

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule