• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሲና የተረፉት የሲኦል ነዋሪዎች ጩኸት!!

October 26, 2012 12:29 pm by Editor 6 Comments

“ላለፉት ሶስት ዓመታት ማንም ሳያውቀን ታስረናል። አሁን ጉዳያችን ለዓለም መድረሱን ሰማን።የተፈታን መስሎናል” የሚሉት እስራኤል ራምሌ በሚባ እስርቤት ከሶስት ዓመት በላይ ታስረው ያሉት ወገኖች ናቸው። ይህ የሆነው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር በርዕስ ለእስራኤል ጠ/ሚኒስትር በግልባጭ ደግሞ ከጉዳዩ ጋር አግባብ ላላቸው ለተለያዩ የአገሪቱ ባለስልጣናት፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የመገናኛዎች አውታሮች ያሰራጩትን ደብዳቤ ተከትሎ በእስር ላይ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በመንቀሳቀሱ ነው።

በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማኅበር ሊቀመንበር አቶ ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ ለጎልጉል እንዳስታወቁት ከእስር ቤት በስልክ ያነጋገሯቸው ወገኖች የደብዳቤውን መልዕክት ሰምተው አስታዋሽ በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። አቶ ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው “ማድረግ የሚገባንን ማከናወን ጀምረናል የሚሆነውን እናያለን” በማለት በቅርቡ ከእስራኤል መንግስት ባለስልጣናት ጋር ለመነጋገር ወደ ስፍራው እንደሚያመሩና እስር ላይ የሚገኙትን ወገኖቻቸውን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።

ኦክቶበር 16 ቀን 2012ዓም በኢትዮጵያ ወቅታዊ የመወያያ (ECADF) የፓልቶክ መድረክ አንድ እንግዳ ቀርቦ ነበር። ጠያቂዋ ሙያዬ ምስክር መናገርና መጠየቅ ተስኗት አምላኳን እየተማጸነች ድምጿ ጠፋ። በሱዳን በኩል በስደት ካገራቸው የሚወጡ ኢትዮጵያዊያን በሲና በረሃ የደረሰባቸውን አሰቃቂ ግፍ የሚናገረው ወጣት ፍቅሩ፣ በረሃ ላይ ስለሚደርስባቸው ዘግናኝ ግፍ ሶስት ዓመት ከሶስት ወር ከታሰረበት እስር ቤት ውስጥ የኑዛዜ ያህል የወገኖቹን ስቃይ አስተጋባ።

ራምሌ እስር ቤት

በረሃ ውስጥ የሚያገኟቸው አረቦች ገንዘብ ሲያጡ ኩላሊታቸውን ይወስዳሉ። አንዳንዴም አራትና ሶስት በመሆን “የኔን ውሰደው እነሱን ተዋቸው” በማለት ራስን ለእርድ የሚያቀርቡ ወገኖች አሉ። ኩላሊትና ልብ ለመልቀም ከጎረቤት አካባቢ እንደሚመጡ የተቆሙት የህክምና ባለሙያዎች የአካል ክፍላቸውን አውልቀው የወሰዱባቸው ወገኖቻችንን አካላቸው ተወስዶ ሲያበቃ አምጥተው ይዘረግፏቸዋል። ከአስራ አራት እስከ አስራ ስድስት ዓመት የሚሆናቸውን ታዳጊ እህቶቻችንን ክብራቸውን በመከራ ውስጥ ተገስሰዋል። ከዚህ ሁሉ መከራና ሞት ተርፈው ከለላ ፍለጋ እስራኤል የገቡት ወገኖች የገጠማቸው ህይወት እጅግ አሳዛኝ ነው።

አቶ ሳሙኤል እንደሚሉት የኢትዮጵያውያኑ መታሰር እንዲታወቅ አይፈለግም ነበር። ተገደው ማመልከቻ በመጻፍ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ከተደረጉት ውጪ በእናታቸው እቅፍ ላይ ያሉትን ጨምሮ ከሶስት መቶ በላይ ወገኖች በጠረፍ ድንኳን ውስጥ ከታሰሩ አራትና ሶስት ዓመታትን አስቆጥረዋል።

አቶ ኦባንግ ከሁሉም በፊት የሚያነሱት ነጥብ “ለኢትዮጵያዊያን አዲስ ኢትዮጵያ ትሰራለች።አሁን ስደት ላይ ያሉት ወገኖች የጠየቁት ጊዜያዊ ከለላ ነው። በ1997 የጄኔቫ ኮንቬንሽን መሰረት ጉዳያቸው ሊጣራ ይገባል” የሚል የህግ ጥያቄ ነው። አቶ ሳሙኤልም አቶ ኦባንግ የሚሉትን ይጋራሉ።

በእስር የሚማቅቁት ወገኖች ድምጽ ይፋ መሆኑን ተከትሎ አቶ ኦባንግ የጻፉት ግልጽ ደብዳቤ ግልባጭ የተደረገላቸው ታዋቂ የሚዲያ አካላት ስፍራው ድረስ ይደርሳሉ፣ እስረኞቹን አነጋግረውና ጎብኝተው የደረሰባቸውን በደል ለዓለም ያጋልጣሉ የሚል ፍርሃት መፈጠሩን፣ ለዚህም አንዳንድ ምልክቶች መታየታቸውን አቶ ሳሙኤል አለባቸው ይናገራሉ። ለጉዳዩ ቅድሚያ የሰጡትን ሚዲያዎችና ተቋማት በማመስገን ጥሪ የሚያስተላልፉት አቶ ሳሙኤል “በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚሰሩ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ድርጅቶች፣ ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ አገርና ወገን ወዳዶች…” ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያሰራጨውን ግልጽ ደብዳቤ በመደገፍ ጫናውን እንዲያበረቱ ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ኦባንግ በጋራ ንቅናቄው በኩል አቤቱታ (ፒቴሽን) እንዲያስፈርሙም ተጠይቀዋል። በግል መልዕክት የላኩላቸው ክፍሎች እንዳሉም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያዊ ስደተኞች በኬንያ፣ በጃፓን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ እስራኤል፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ … በመሳሰሉት አገሮች ለሚደርስባቸው በደል “አገራችሁ እንደ ሶማሊያና ኤርትራ አይደለችም እያሉ የተባበሩት መንግስታትን መመሪያ ይጠቅሳሉ” የሚሉት አቶ ኦባንግ ድርጅታቸው (አኢጋን) ወደ ጃፓን፣ ሜክሲኮ፣ ኖርዌይ፣ ማልታ፣ ስዊድን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ … የተጓዘውና መልዕክተኛ የላከው ይህንን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር እንደሆነ አመልክተዋል።

በሌሎች የዓለም ክፍሎች እንዳደረጉት ሁሉ በቅርቡ የጋራ ንቅናቄው በአካባቢው ከሚገኙ ቅርንጫፍ (ቻፕተር) አመራሮች ጋር በመነጋገር ወደ እስራኤል በመጓዝ ከሚመለከታቸው የእስራኤል ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ ያስታወቁት አቶ ኦባንግ “የትም ይሁን የትም፣ የየትኛውም ብሄር አባል ቢሆን፣ ህጻናትም ሆኑ አዋቂዎች ኢትዮጵያዊያን ሁላችንም አንድ አካል ነን። ከታሰሩ ሁላችንም ታስረናል፣ ከተገረፉ ሁላችም ያመናል፣ ከተራቡ ሁላችንም ይርበናል፣ ሲጠሙ ሁላችንም ይጠማናል። የአንድ ወገናችን ስቃይ የሁላችንም ስቃይ በመሆኑ አቅማችን በፈቀደ ሁሉ የሚቻለንን ለማድረግ ዝግጁ ነን” ብለዋል። ይህ አስተሳሰብ “ሁላችንም ነጻ ካልወጣን ማንም ነጻ አይወጣም” ከሚለው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መሰረታዊ መርህ የሚነሳ መሆኑንም አመልክተዋል።

በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ወገኖቻችን እየተሰቃዩ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ በቅርቡ ታላላቅ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት፤ ሂውማን ራይትስንም ጨምሮ ወደ እስራኤል፣ ሲና በረሃና ኬንያ እንደሚጓዙ አመልክተዋል፡፡ አቶ ኦባንግ ከተቋማቱ ጋር ድርጅታቸው በተለይ ስለሚሰራው ሥራ አላብራሩም።

የተጀመረውን ዘመቻ ተከትሎ “ትምህርት እናስተምራቸዋለን” በሚል ህጻናትን ወደ ሌላ ስፍራ ማዘዋወር መጀመሩን፣ የእስራኤል ባለስልጣናት የጉብኝት ቀጠሮ መያዛቸውን፣ ያመለከቱት አቶ ሳሙኤል፣ አቡነ መርቆሪዎስ ስደተኞቹን ባሉበት ቦታ በመገኘት ለመጎብኘት ጊዜ መያዛቸውን ተናግረዋል። በልዩ ሁኔታ ጉብኝታቸውን ለማዘጋጅት ሙከራ እያደረጉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
“በፍርድ ቤት የተፈረደበት እስረኛ ፍርዱን ሲጨርስ እንደሚለቀቅ ስለሚያውቅ ቀኑን ይጠብቃል። የእኛ አይታወቅም። እኛ ያለነው መደበኛ እስር ቤት አይደለም። ዓለም በቃኝ ነው…” ፍቅሩ ከሙያዬ ምስክር ጋር ባደረገው አሳዛኝ ቃለ መጠይቅ ወቅት የተናገረው ቃል ነው። ከሲና በረሃ ስቃይ በኋላ ሌላ ሲኦል!! ኦባንግ ሜቶ “ለሁላችንም መፍትሄ የምትሰጥ አገር አለችን። እሷም አዲሲቷ ኢትዮጵያ ናት። መሰረቷም ቅድሚያ ለሰብዓዊነት ይሆናል። አዲሲቷ ኢትዮጵያ እስክትሰራ ባለንበት ልንከበርና ችግራችንን ተገንዝበው ሊያስተናግዱን ይገባል” ይላሉ።

በተመሳሳይ ዜና አቶ ኦባንግ በኖርዌይ ስለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ለመነጋገር ወደ ኦስሎ ያመራሉ። በኖርዌይ የሚገኙ ስደተኞች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ በየጊዜው የሚደረግባቸው ጫና እንዲቆም በየአቅጣጫው ጥረት ሲደረግ መቆየቱ በተለያዩ መገናኛዎች መገለጹ አይዘነጋም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Ethiopia, Full Width Top, israel, Middle Column, Obang, refugees, SMNE

Reader Interactions

Comments

  1. Tariku says

    October 27, 2012 01:08 am at 1:08 am

    i just want to say thank you for this article!
    b/c i am one of them!

    Reply
  2. Jibrel says

    October 27, 2012 07:31 am at 7:31 am

    Meche new yeethiopiawi enba emikomew?nafekegn hizebu nuro almola bilot akalu eyegodele beyebereha yikeratetal yeweyane balesiltan lijoch chaina..europa..america talalak timehiret bet wist yimaralu minew habesha?edih fezezin lemin 1honen aninesam?bianes nege lijochachin emaysededubat ethiopian enifter …..

    Reply
  3. dawit says

    October 27, 2012 10:04 am at 10:04 am

    አቶ ኦባንግ ምስጋና ይሁንልዎ! በዚህ አሳዛኝ ጽሁፍ ውስጥ የተጠቀሱት ወገኖች ይህ ሁሉ መከራ ሲደርስባቸው፣ለአራትና ከዚያም በላይ ዓመታት ባስከፊ ሁኔታ መታሰራቸው አለመሰማቱ ልብ ያደማል። አንደኛው ተናጋሪ እንደተናገሩት ሁሉም በሚችለው መጠን፣ መድረስ በሚችልበት ቦታና ማድረግ የሚችለውን በማድረግ ለወገኖቹ ይጩህ፣እንጩህ፣ አንድ ነገር ተደርጎ ባስቸኳይ የሚጎበኙበት ሁኔታ የሚመቻችበትን ሁኔታ ማፈላለግ ይቻል ዘንድ ሚዲያዎች ይበልጥ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል። አቶ ኦባንግ ሜቶ ብቻቸውን ላደረጉትና እያደረጉ ላሉት ትግል በድጋሚ አክብሮቴን ለመግለጽ እወዳለሁ።

    Reply
  4. solo says

    October 28, 2012 12:09 am at 12:09 am

    አቶ ኦባንግ በርታ ሁላችንም ድምጻችንን እናስማለን !

    Reply
  5. Hager says

    October 28, 2012 04:46 pm at 4:46 pm

    It is heart touching news. Thank you Mr. Obang

    Reply
  6. yeshitela zenebe says

    October 31, 2012 12:47 pm at 12:47 pm

    Dear Ato Obang Metho, we thank you very much for all the efforts you are putting for the respect and freedom of all Ethiopians inside and outside Ethiopia. You have shown a decisive leadreship for the respect of human rights. Ethiopians respect your patriotic actions to defend our god given rights. As you always spoke about “no one is free untill all are free” and “Humanity befor ethnicity” are clearly defines that we all need to unit and fight for. We stand beside you for the respect of our basic human rights. God Bless you Ato Obang.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule