• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአንድ ሳምንት ሁለተኛ አደጋ!

July 19, 2013 12:56 am by Editor 2 Comments

ከአዲስ አበባ ወደ አክሱም ይጓዝ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ረቡዕ ለት በጭንቅ እንዲያርፍ መደረጉ ተገለጸ፡፡ አደጋው ከአምስት ደቂቃ በፊት ቢከሰት ኖሮ አውሮፕላኑ አየር ላይ እያለ ሊፈነዳ ይችል እንደነበር ባለሥልጣናት አስታወቁ፡፡

78 መንገደኞችንና ሠራተኞችን አሣፍሮ ይጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ (Bombardier Q400) አውሮፕላን ከክንፎቹ በአንዱ ጭስ መነሣቱን የሚጠቁም ማስጠንቀቂያ በመደወሉ እጅግ አስጨናቂ በሆነ መልኩ እንዲያርፍ መደረጉን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ ጋዜጣው ስማቸው ከመግለጽ የተቆጠቡ ባለሥልጣንን ጠቅሶ እንደጻፈው አውሮፕላኑ ከማረፉ ከአንድ ደቂቃ በፊት የግራው ክንፍ እየጨሰ መሆኑን ማስጠንቀቂያው ማመልከቱንና አንዱ ሞተር ደግሞ እንደሚገባው ይሰራ እንዳልነበረ ገልጸዋል፡፡

ሱዳን ትሪቢዩን በስልክ ያነጋገራቸው ተሳፋሪ ጭስ ከአውሮፕላኑ ክንፍ ሲወጣ መመልከታቸውን፤ ተሳፋሪው ሁሉ በጭንቅ ውስጥ የነበረ መሆኑንና ሁኔታው በጣም አስደንጋጭ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን በመጥቀስ የአየር መንገዱ ባለሥልጣናት እንደሚሉት ከሆነ አደጋው አውሮፕላኑ ከማረፉ አምስት ደቂቃ በፊት ተከስቶ ቢሆን ኖሮ አውሮፕላኑ አየር ላይ እያለ ሊፈነዳ ይችል ነበር፡፡

ሁኔታውን በጥንቃቄ ያስተዋለው የአውሮፕላኑ አብራሪ ካፒቴን ፈጣን እርምጃ በመውሰድ አውሮፕላኑ ወደ ዋናው ማቆሚያ ከመድረሱ በፊት በማቆምና ተሣፋሪዎቹ በፍጥነት እንዲወጡ በማድረግ ሊከሰት የነበረውን የእሣት አደጋ መከላከሉ ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ የካፒቴኑ ውሳኔ የሚደነቅ መሆኑን ባለሥልጣናቱ የገለጹ ሲሆን ተሣፋሪዎቹም ህይወታቸውን ከአደጋው በመታደጉ የጀግና ክብር በመሥጠት ማመስገናቸው ጨምሮ ተጠቅሷል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለሥልጣናት የጭሱ መነሻ እየተመረመረ ነው ቢሉም አየር መንገዱ አደጋውን አስመልክቶ እስካሁን ይፋዊ መግለጫ አላወጣም፡፡

ባለፈው ሳምንት በቆመበት እሣት የተነሳበት ሌላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋው ከታወቀ ጀምሮ የውጭ አገር የዜና ወኪሎች በየደቂቃው ዘገባ ሲያቀርቡበት የነበረ መሆኑ ቢታወቅም ከዚህ በባሰ መልኩ በርካታ ተሣፋሪዎችን ጭኖ ለአደጋ ተጋልጦ የነበረው አውሮፕላን ጉዳይ አደጋው ከተከሰተበት ረቡዕ ጀምሮ እስካሁን በመንግሥትም በኩል ሆነ በአየር መንገዱ ይፋ አለመሆኑ በበርካታዎች ዘንድ ጥያቄ መጫሩ የማይቀር ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    July 20, 2013 06:05 pm at 6:05 pm

    ውድ ጎልጉል፣ የአየር መንገዱ አስተዳደርና መንግሥት በወሰዳቸው እርምጃዎች ምክንያት እየተከሰተ ያለ ችግር ነው። አንደኛ፣ ጥራት ያላቸው አብራሪዎችና ሜካኒኮች ለቅቀው እንዲሄዱ ተደርጓል። ጥያቄ ማንሳት መንግሥትን እንደ መቃወም ስለ ተቆጠረ የተከለከለ ነው። ስለዚህ ጥራት ቀንሷል። ሁለተኛ፣ ሠራተኛው ተመጣጣኝ ደመወዝ ሳይከፈለው ረጅም ሰዓት እንዲሠራ እየተገደደ ነው። ሦስተኛ፣ የአየር መንገዱን ቁልፍ ቦታዎች [ከቦርድ አባልነት ጀምሮ] የያዙት መንግሥት የመደባቸው [አብዛኛው ከትግራይ] እንጂ ብቃት ያላቸው አይደሉም። በምሥጢር ለመውጣትና ለመግባት፣ ገንዘብ ለማውጣትና እቃ ለማስገባት እንዲመች ቁልፍ ቦታዎች ላይ ከገዥው መደብ የሆኑ ብቻ ተመድበዋል። በስፖርት ፌዴሬሽን የተከሰተው ይኸው ነው። ቴሌኮሙኒኬሽን ብትሄድም ይኸው ነው።

    Reply
  2. አለም says

    July 20, 2013 06:18 pm at 6:18 pm

    አደጋ ሲደጋገም ግን አየር መንገዱ ተፈላጊነቱ እንደሚቀንስ የታሰበ አይመስልም። በንግዱ ዓለም አንዴ ከወደቁ መነሳት እጅግ ከባድ ይሆናል። በተጨማሪ የሰውን ሕይወት ለአደጋ የተጋለጠ ያደርገዋል። አቶ ግርማ ዋቄ ከአረብ አገር ተጠርተው የመጡት ችግር ስለ ተፈጠረ እንዲያቃኑት ነው። አንዴ ተቃንቶ ማትረፍ ሲጀምር በጡረታ አሰናብተዋቸው የራሳቸውን ሰው [ተወልደን] ሾሙ። በቅድሚያ ግን ተወልደን እንዲያሠለጥኑ ተደረገ። ከተወልደ የሚሻሉ ብዙዎች አሉ። ግን አልተፈለጉም። በጡረታ ሰበብ የተገፉት አቶ ግርማ ባሁኑ ወቅት የሩዋንዳን አየር መንገድ እያደራጁ ይገኛሉ። የተወልደን ብቁ አለመሆን ለመሸፋፈን ስንት ጊዜ ይህን ሽልማት ተሸለመ እየተባለ እንደ ሆነ ጉግል አድርጋችሁ እዩ። በሊባኖስ ላይ የፈነዳው ጉዳይ ተደባብሶ ለምን እንደ ቀረ ማን አወቀ? ኢትዮጵያውያንን እንደ ብቃታቸውና በዜግነት መብታቸው አለማሳተፉ ይህ መንግሥት ከፈጸማቸው ግፎች የመጀመሪያውን ደረጃ ይይዛሉ። ይኸን የምለው ስለ ጥላቻ አይደለም። ቁጭ ብዬ አጣርቼ ሐቁን ለማወቅ ጥረት አድርጌ ነው። በየመ/ቤቶች ቁልፍ ቦታ የያዙትን ስምና ችሎታ ገምግሜ ነው። አሳፋሪ ሥራ እየተደረገ ነው። ከየብሔሩ እኩል ዕድል ለመስጠት ነው እያሉ ያታልላሉ። ጎልጉሎች ምን ይመስላችኋል?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule