• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መናገርና መፃፍ ወንጀል የሆነባት ሃገራችን

April 2, 2014 07:22 pm by Editor Leave a Comment

ከአመታት በፊት በአዲስ አበባችን ውቧ ቅዳሜን በውቧ አዲስ ነገር ጋዜጣ በምናጣጥመበት ግዜ አንድ በጣም የማከብረው አምደኛ በኢትዮጲያ ስላለው የጋዜጠኝነትና የመፃፍ ነፃነት ያለው ቃል በቃል ባይሆንም በጥቅሉ ይህ ነበር፣

“ . . . በኢትዮጲያ የጋዜጠኝነት ሞያ በአግባቡ የተተገብረው እንዲሁም  በነፃነት መፃፍና መተንተን የሚቻለው ስለ አውሮፓ እግር ኳስ በተለይም ስለ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት ነዳጅ ጨመረ ፖለቲካ ነው ፣ ነዳጅ ቀነሰም ፖለቲካ ነው ፣ ኑሮ ተወደደ ፖለቲካ ነው ፣ ታክሲ ጠፋ ፖለቲካ ነው ፣ ምርጫ ደረሰ ፖለቲካ ነው ፣ ሁሉ ነገር ፖለቲካ ነው። ታዲያ በጋዜጠኝነት የተመረቁ ፣ በፅሁፍና በትንተና የተካኑ ስለምን ይፃፉ ሰው መቼም ቋንቋ እያለው ሳያወራ ፣ ሳይፅፍ አይኖር . . . “

ይህ ፀሃፊ ያለው እውነቱን ነው አብዛኛው የሃገራችን ህዝብ በተለይም ወጣቱ (እኔንም ጨምሮ) ለአድማጭ በሚስማማ መልኩ በሚያምር ቋንቋና አቀራረብ እየተመጠነ የሚቀርበው የአውሮፓ እግር ኳስ መረጃ ኢትዮጲያውያን ከአንድ አውሮፓዊ ባልተናነሰ መልኩ ስለ አውሮፓ እግር ኳስ እውቀትና ፍቅር እንዲያድርብን አድርጓል። (ይህ ማለት እንግዲህ የሃገራችን ህዝብ ክጅምሩ ያለውን በወገንተኛነት ላይ ያልተመሰረተ ንፁህ የእግር ኳስ ፍቅር ሳንረሳ ማለት ነው)

የሆነው ሆኖ ዋናው ይህችን ፅሁፍ የጀመርኩበት መነሻዬ በሃገራችን የጋዜጠኝነትና የመፃፍ መብት የስፖርቱን አንድ መቶኛ ያህል እንኳን ቢፈቀድና ከስፖርቱ ውጪ ስለሌላ ነገር መፃፍ የሚያሰቅል ወንጀል ባይሆን የሃገራችን ህዝብና ወጣት ስለ በጎ የዲሞክራሲ ስርዓት ጥቅምና አስፈላጊነት ፣ ስለማህበረሰባዊ አንድነት ፣ ስለ መልካም አስተዳደር ፣ ስለ ሃገር ፍቅርና እድገት እንዲሁም ስለበርካታ ጠቃሚ ነገሮች በነፃነት እየተፃፈና እየተወያየን የሃገራችን ከድህነት መውጫ ቀናት በተቃረበልን ነበር። ያለው እውነታ ግን ዜጎች ስለሚኖሩት ኑሮ እንኳን በነፃነት አይደለም በሹክሹክታ ማውራትም እንደ ችግር ፈጣሪነት እየተቆጠረ ነው።

በሃገራችን በተለያዩ የመንግስት ስልጣናት ላይ ተቀምጠው ህዝብን የማገልገል ሃላፊነት ወደጎን በመተው ስልጣኑን ለግል ጥቅማቸው በግድ ይዘው እንደልባቸው ያሻቸውን በማድረግ እየኖሩ “እንዴት በጋዜጠኛ ፣ በፀሃፊና በማህበራዊ ሚዲያዎች ስሜ ተነሳ” ብለው “ሃገር ይያዝ” የሚሉ ሃላፊነት የጎደላቸው የመንግስት ባለስልጣናት ጥቂት አይደሉም። ገና ምኑን አይታችሁት በሉልኝ።

ባደጉ ሃገራት የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የጋዜጠኝነት ፣ የመፃፍና የሚዲያ ነፃነት ምን ያህል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያረግ እንዲሁም በዲሞክራሲ ላይ በተመሰረት የሃገር አገዛዝ የመፃፍ ፣ የመናገርና የነፃ ሚዲያዎች መኖር ምን ያህል ታላቅ በጎ ሚና እንደሚጫወት የዲሞክራሲና አገዛዝ ታሪካቸው ያትታል። ነገር ግን እንደሃገራችን ኢትዮጲያ አይነት የዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር ስርዓት ይቅርና እጅግ መሰረታዊ የሚባሉት ሰብዓዊ መብቶች በእንጭጩ የቀሩባት ሃገር መናገርና መፃፍ እንደወንጀል እየተቆጠረ ነው። ሀገርንና ህዝብን አስተዳድራለው ብሎ ከዜጎች ይሁንታ ውጪ ስልጣኑን የተቆጣጠረው እንደ ህወሃት መንግስት ያለ አምባገነናዊ ስርዓት እንዴት ስሜ በጋዜጠኛና ፅሁፍ ይነሳል ብሎ ለሃገርና ለህዝብ ኑሮ መሻሻል በጎ እሳቤ ያነሱ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባትና ለሃገር ማደግ በጨዋነት እይታቸውንና እውቀታቸውን ለማካፈል ብዕራቸውን ያነሱ ሁሉ እየሰበሰቡ በየእስር ቤቱ ማጎር ፣ የማህበራዊ ዲሞክራሲያው እሳቤዎች መወያያ መድረኮችን ማፈን ምን ይሉታል?

በአንድ ሃገር የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የዜጎች በሰብዓዊ መብት ፣ በዲሞክራሲ ፣ በፖለቲካ እንዲሁም በህዝብና ሃገር አስተዳደር ዙሪያ ያላቸው ንቃተ ህሊና የሚጫወተው ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው። የሲቪክና የፖለቲካ ማህበራት ፣ የጋዜጠኞችና የነፃ ሚዲያዎች መብዛትና ተሳትፎ የማህበረሰብ በዘርፉ ያለውን ንቃተ ህሊና መጨመሪያ መሆናቸው አሌ የማይባል ሃቅ ነው። ነገር ግን ዘርፉን በበጎ መልኩ አይቶ ከማበረታታት ይልቅ ህዝብን ለማስተዳደር የተያዘን ስልጣንንና ጉልበት ለዚሁ ዘርፍ ተግዳሮት ማዋል ግን የለየለት ፀረ ዲሞክራሲያዊ ወንጀል ነው።

የህወሃት መንግስት በግድ ለህዝቡ እኔ አውቅልሃለው ፣ እኔ የምለውን ብቻ ዝም ብላችሁ ተቀበሉ የሚል ያረጀ ያፈጀ የማናለብኝነት ድርጊት ከግዜ ወደ ግዜ እየባሰበት ነው። የኢትዮጲያ ህዝብ የሚበጀውንና የማይበጀውን አይቶ ፣ አመዛዝኖ እንዲሁም አጣርቶ ማወቅ የሚችል የበሰለ ህዝብ ነው። ህዝባችን የተፃፈ ሁሉ እያነበበ በስሜት የሚነዳ ህዝብ አይደለም። በርካቶቻችን ከምናስበው በላይ  የሚሆነውንና የሚጠቅመውን በሚገባ ያውቃል። ነገር ግን የህወሃት መንግስት ለብዙ ሃገርና ህዝብ ጠቃሚ ነገሮች ሊውል የሚችል በሚሊዮን የሚቆጠር የሃገር ሃብት የተለያዩ ሚዲያዎችን ለማፈንና ለመሰለል ሲውል እጅግ ያሳምማል። ይህ ድርጊት በውሸትና በተራ ፕሮፓጋንዳ የተሞላውን የመንግስት ሚዲያ በግድ በህዝብ ጆሮ እንዲደርስ በማድረግ ዜጎች ስለሚወዷትና ስለሚኖሩባት ውድ ሃገራቸው አገዛዝና ኢኮኖሚ ስርዓት የግል አስተያየታቸውን እያነሱ በተለያዩ መወያያ መድረኮችና ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዳይወያዩ ማድረግና የወንጀል ያህል እንዲቆጠር ማድረግ ዜጎችን በገዛ ሃገራቸው ባይተዋር የማድረግ ሂደት አንዱ ዋነኛ የህወሃት መንግስት ስራ ሆኗል።

የህወሃት መንግስት ከሌሎች አምባገነናዊ መንግስታት የሚለየውና የባሰ ያደረገው ደግሞ ስለህዝብና መንግስት አስተዳደር በጎ ግንዛቤ የሚያስጨብጡ ሚዲያዎችን ማፈኑና መከልከሉ ብቻ ሳይሆን ህወሃት እንደጦር ከሚፈራው የዲሞክራሲ ምንነት አስገንዛቢ ሚዲያዎች ባሻገር ዜጎችን እያዝናኑ የተለያዩ የኑሮ ክህሎትና እውቀት የሚያስጨብጡ ሚዲያዎችን አለምፍቀዱም ነው። አማራጭ የፖለቲካ ስርዓት አመንጪ አካላት ለህዝብና ለሃገር የሚጠቅሙ እሳቤዎችን ህዝብ ጆሮ አለማድረሳቸው ከሚፈጥረው ጉዳት ባሻገር በተለያዩ ያደጉ ሃገራት ለዜጎች ከፍተኛ ጥቅም በመስጠት የሚታወቁትን የህዝብን ንቃተ ህሊና የሚያዳብሩ እንዲሁም የኑሮ መላ የሚያቀብሉ በጎ ሚዲያዎችን ከህዝብ እይታና እውቅና ውጪ ማድረግ እጅግ የሚያሳምም ወንጀል ነው።

ናትናኤል ካብቲመር
ናትናኤል ካብቲመር

በዚህ የቴክኖሎጂ ዘመን የሰብዓዊ ፍጡርን ስለሚኖረው ህይወትና ስለሚኖርበት ሃገር ያለውን አስተያየትና አመለካከት እርስ በርስ እንዳይካፈል ማገድ ፀረ ዲሞክራሲያዊነት ብቻ ሳይሆን ፀረ ተፈጥሮ መሆንም ነው። የዜጎችን ድምፅ አለልክ ማፈንም የስርዓቱን መጨረሻ ማፋጠን መሆኑን ህወሃቶች ሊረዱት ይገባል። በተጨማሪም ሊረዱት የሚገባው ነገር የጨቆኑት ህዝብ ከሚያስቡትና ከሚገምቱት በላይ አመዛዛኝና አርቆ አሳቢ መሆኑን የሚነዙት ተራ ፕሮፓጋንዳ ከማሰልቸትና መጨረሻቸውን ከማፋጠን ውጪ ሌላ የሚፈይደው ነገር አለመኖሩን ነው። አሁንም ደግሜ ደጋግሜ የምናግረው ህዝባችን የሚበጀውንና የሚሆነውን በሚገባ ያውቃል። ስለሚወዳትና ስለሚኖርበት ሃገር በነፃነት እንዳይወያይ ማገድ ፀረ ዲሞክራሲያዊ ወንጀል ነው። የህዝብን አመዛዛኝነትና ጨዋነት በሌላ ተርጉሞ በህዝብ ጫንቃ ላይ እንደልብ መሆን መጨረሻውን አጉል ያደርገዋል እላለው።

ህዝባችንና ሃገራችን ለዘላለም ይኑሩልን!!!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule