• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”

January 9, 2013 02:03 pm by Editor 3 Comments

በበርካታዎች ዘንድ የተለያዩ ስሞች አሏቸው፤ የአደባባይ ምሁር፣ አንጋፋ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ፣ ጋሼ መስፍን፣ ወዘተ፡፡ በእኛ ግምት ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ የሚለው ገጣሚ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በተለይ በቅርብ ዓመታት ያሳተሟቸው መጻህፍት፣ የጻፏቸው ጦማሮች፣ ወዘተ ይህንን ማዕረግ ሊያሰጥዋቸው ይችላሉ ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡

ፕ/ር መስፍን በህይወት ዘመናቸው ካስተማሩትና ካስተላለፉት ዕውቀት በተጨማሪ እጅግ በርካታ መጻህፍትን በማሳተም ይህንን ለዘመናት የዳበረውን ዕውቀታቸውን ለመጪው ትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ አራት መጻህፍትን አሳትመዋል፡፡ በመጪው ሚያዚያ ወር 83 ዓመታቸውን ከማክበራቸው በፊት ባለቅኔው መስፍን በሰማኒያዎቹ ዕድሜያቸው ይህንን ሁሉ ለማድረግ መብቃታቸው ከጻፉት መጻህፍትና አርቆ አሳቢነታቸው በተጨማሪ በአድናቆት ሊጠቀስ የሚገባው የመንፈስ ጥንካሬ ነው፡፡

በመጻህፍትና በመጽሔት ብቻ አልተወሰኑም፤ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ከወጣት እስከ ጎልማሳ ምሁራን በብዛት የማይጠቀሙበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመገልገል አስተዋዩ መስፍን በራሳቸው ብሎግ ላይ ጦማራቸውን እያተሙ በየጊዜው ያስተምሩናል፤ የወደፊቱን አበሳ እንድንወጣ ሥራቸውን ለዘመኑ ወጣት በፍጥነት ያስተላልፋሉ፡፡ ምክንያቱም ለመስፍን “ዝምታ ወርቅ” አይደለም፤ “አያገባኝም” ማለትም መፍትሔ አይደለም፡፡

የአገራችን ታሪክ ፈጽሞ እየተዛባና መስመር እየለቀቀ፤ የሕዝባችን ሞራልና ሰብዓዊነት ዕርቃኑን እየቀረ፣ እጅግ በርካታ ባዕድ ነገሮች እንደ ኢትዮጵያዊ ባህል ለዘመናት እየተጨመሩ ባለበት ባሁኑ ወቅት ፕ/ር መስፍን የሚያሳትሟቸው መጻህፍት በዕድሜያቸው ያካበቱትን ልምድ ለአሁኑ ዘመን ትውልድ ዋቢ ይሆን ዘንድ የተጻፉ ብቻ ሳይሆኑ በህዝባችን ውስጥ ለዘመናት የተንሰራፋውን ችግር ግልጽና ማንም ሊያስተውለው በሚችል መልኩ በትነው የሚስተምሩ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ችግሩ ብቻ አይደለም የሚጽፉት፤ መፍትሔውን ጭምር እንጂ፡፡ “ነቢይ በአገሩ አይከበር” እንደሚባል የአገራችንን አዋቂዎች ድንቅ ሥራዎች ቸል እያልን ወደምዕራባዊያንና ሌሎች የባዕድ ቋንቋ ሥራዎችና ትምህርቶች በማተኮራችን መሠረታዊውን የአገራችንን ችግር በውል ለመለየትና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ቸግሮናል፡፡

ከውጪ በቀጥታ በተቀዱና ለኢትዮጵያውያን ባህልና አኗኗር ፈጽሞ ባዕድ የሆኑ የፖለቲካ አመለካከቶችን በህዝባችን ላይ ተጭነው የሚናገረውን የማያውቅ ሰባኪ ቋንቋውን ለማያስተውል ሕዝብ ሲሰብክ ስንት ዘመን አለፈ?! ችግሩ መጫኑና ከሌሎች መቀዳቱ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ እንዲሆን አለመደረጉ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ የሥልጣኔ ዕድገት፣ ታሪክ፣ ባህል፣ … እንዲመጥን ተደርጎ ኢትዮጵያዊ እንዲሆን ሳይደረግ በመቅረቱ ችግሩ ያለው ችግሩ ላይ ይሁን ወይም መፍትሔው ላይ በውል ሳይታወቅ የሥልጣኔ ቀደምት የነበርን የዓለም ጭራ ሆነናል፡፡ ፕ/ር መስፍን እንደሚሉት ሥልጣንን መግራት አቅቶናል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ የታተሙት የፈላስፋው መስፍን መጻሕፍት “ሥልጣን፤ ባህልና አገዛዝ፤ ዴሞክራሲና ምርጫ”፤ “የክህደት ቁልቁለት” እና “አደጋ ያንዣበበበት የአፍሪካ ቀንድ” ከላይ የጠቀስናቸውን ብቻ ሳይሆን እጅግ ሰፋ ያሉና ጥልቀት ያላቸውን የአገራችንን ጉዳዮች ይዳስሳሉ፡፡ የችግራችንን ምክንያትና ምንጭ ያስረዳሉ፡፡ ግልጽና ለማንም የማያሻማ መፍትሔ ይሰጣሉ፡፡

ሰሞኑን ያሳተሙት “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ” የሚለው መጽሐፍ ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር የሚያውቅና አማርኛ የሚያስተውል ሁሉ ሊያነበው የሚገባ ነው፡፡ “ለምን ግን እኛ ኢትዮጵያውያን እንዲህ ሆንን?” ብሎ የሚጠይቅ ሁሉ የከሸፍንበትን ምክንያትና በየትኛው መስክ እንደከሸፍን ለማወቅ ይህ መጽሐፍ ለዘመናት ሲመኘው የነበረ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ መጽሐፉ ሲጀምር ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ እንዲህ በማለት

ቁም! በመጀመሪያ ለአንባቢው አንድ ማስጠንቀቂያ ልስጥ፤ መጽሐፉ በጠቅላላ፣ በተለይም ይህ መቅድም የከረረ ንዴት መግለጫ ነው፤ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ሁኔታ ያልተናደደ፣ የማይናደድና ያልተበሳጨ፣ ወይም ደልቶት የሞቀው ይህንን መጽሐፍ፣ በተለይም ይህንን መቅድም አያንብበው፤ የረጋውን መንፈሱን ያስሸብረዋል፡፡

ፕ/ር መስፍን መጽሐፍ በማሳተም ለመበልጸግ የሚመኙ ሰው እንዳልሆኑ የሚያስተውል ሁሉ ይህንን መጽሐፍ እዚህ ላይ ማስተዋወቃችን የትርፍ ጉዳይ ሳይሆን ለአገራችንና ለወደፊት ትውልድ ከማሰብ እንደሆነ ለማሳሰብ የሚያስፈልግ አይመስለንም፡፡ ስለሆነም መጽሐፉም ሆነ ሌሎች መጽሐፎቻቸውን በአሜሪካ አገር ትርፍ ላይ መሠረት ባላደረገ ነገር ግን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ሙያው የሚጠይቀው ወጪ ወጥቶባቸው ታትመው ስላሉ በቀጥታ ከአሳታሚዎቹ ወይም ከሕጋዊ ወኪሎቻቸው መግዛት አንድኛው የዜግነት ግዴታ እንደሆነ በግልጽ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ በተለያየ መልኩ በርካሽና ጥራቱን ባልጠበቀ ሁኔታ እያሳተሙ ለጥቂት ትርፍ መሯሯጥና ህጋዊ ሻጭ መስሎ የራስን ኪስ ለማደለብ መሞከር አንዱ የሥነምግባር ውድቀታችንና የመክሸፋችን ምልክት ነውና ህገወጥ ሥራን አናደፋፍር፤ በገሃድ ስናይም እንቃወም፡፡ ጥቂት ብሮችን ለማትረፍ ኅሊናችንን አናሸቅጠው!

አዲሱ መጽሐፍ “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”እና ቀደምት የፕ/ር መስፍን መጽሐፍቶች በሚከተሉት መንገዶች ማግኘት ይቻላል፡፡

የመስፍን ወልደማርያም ብሎግ
http://mesfinwoldemariam.wordpress.com/
(617) 543-3462 (ለማንኛውም ጥያቄ ይህንን ስልክ ይደውሉ)

ESAT Store
http://ethsat.com/store/

Tenadam International Market
3817 S George Mason Drive
Falls Church, VA 22041-3763
(703) 933-6038

Dama Restaurant
1503 Columbia Pike
Arlington, VA 22204
(703) 920-3559

Rosalind’s Ethiopian Restaurant
1044 South Fairfax Avenue Los Angeles, CA 90019
(323) 936-2486

Maru Grocery
8353 Park Lane Dallas, TX 75231
(214) 373-6278

Lalibela Cultural Gift Clothing And Variety Store
2257 Massachusetts Ave, Cambridge, MA 02140
(617) 876-2259

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. sintayhu tesfaye says

    February 11, 2013 10:18 am at 10:18 am

    etopyan peopil lov popel

    Reply
    • a says

      March 9, 2013 12:39 am at 12:39 am

      Yes Sintayhu, I agree, we do love people !

      I do appreciate if people strive to bring democracy and good governance to their country, but I wonder why they go to the extent of defacing their own country! To consider an extreme example, we all hate Hitler but we don’t have problem with the Germany.

      Reply
  2. a says

    March 9, 2013 12:41 am at 12:41 am

    (same message as above with minor correction)

    Yes Sintayhu, I agree, we do love people !

    I do appreciate if people strive to bring democracy and good governance to their country, but I wonder why they go to the extent of defacing their own country! To consider an extreme example, we all hate Hitler but we don’t have problem with Germany.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule