• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከዚህ በኋላ ፍ/ ቤት ላለመቅረብ ወስኛለሁ!…”

December 30, 2019 05:56 am by Editor Leave a Comment

(ኤርሚያስ አመልጋ – ከቂሊንጦ)

ድፍን አንድ አመት!…

በህግ ሊያስጠይቀኝ የሚችል ምንም አይነት የወንጀል ድርጊት ባልፈጸምኩበት እና ለክስ የሚያበቃ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ ለእስር ከተዳረግኩና ፍትህ አገኝ ብዬ ፍርድ ቤት መመላለስ ከጀመርኩ እነሆ ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡

የፌዴራል ፖሊስ፣ አቃቤ ህግ እና ፍርድ ቤት በአንድ ሳምባ በሚተነፍሱበት ስርዓት እና አገር ላይ፣ ገለልተኛ ፍርድ እና ሚዛናዊ ፍትህ ማግኘት እንደማይቻል በአንድ አመት የእስር ቤት ቆይታዬ ያረጋገጥኩት ሃቅ ነው!!!

ከዚህ በኋላ ፍትህ አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ራስን ማጃጃል አንደሆነ ተገልጾልኛል፤ አሁን ከስርዓቱ ፍትህ የምጠብቅበት ሳይሆን በእኔ ከደረሰውና ዙሪያዬን ከማየው ተነስቼ የአገራችንን የፍትህ ስርዓት ነውረኛ ባህሪ ለህዝብ የምገልጽበት ወቅት ነው፡፡

“መርምረን እናስራለን እንጂ፣ አስረን አንመረምርም” የተባለለትን የለውጥ ዲስኩርና ፕሮፖጋንዳ ተከትሎ፣ ብዙ ተስፋ የተጣለበት የፍትህ ስርዓት፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ ፍጹም የመንግስት ወገንተኝነቱን እና የአምባገነን መንግስት መሣሪያና መጠቀሚያ ሆኖ መቀጠሉን ለመላው ኢትዮጵያውያንና ለዓለም በድፍረት ማሳወቅ አስፈላጊ መሆኑን ከልብ አምኜበታለሁ፡፡

ከዜጎች ጎን ሆኖ ለእውነት፣ ለፍትህና ለህግ ልዕልና የሚቆም ስርዓት መገንባት ቀጣይ የአገራችን ዜጎች ትልቅ የቤት ስራ መሆኑን በአጽንኦት ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡

ራሳቸውን ከወገንተኝነት ካላጸዱ የፖሊስ፣ የአቃቤ ህግ እና የፍርድ ቤት ተቋማት ጋራ የተጓዝኩበት ረጅም ጎዳና፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ እምነት መጣሌን ትቼ ከመንገዱ ወጣ እንድልና ራሴን በጽሞና እንድጠይቅ አስገድዶኛል፤ አልፎ ተርፎም ከበስተጀርባ በስውር እጆች እየተቀነባበረ የሚሰራብኝ ትልቅ ድራማ እንዳለ ግልጽ አድርጎልኛል፡፡

ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንደገለጽኩት፣ ከኢምፔሪያል ሆቴል ሽያጭ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቃለ-መጠይቅ እፈልግሃለሁ ብሎ ሲጠራኝ፣ ጥሪውን አክብሬ በመሄድ ስለጉዳዩ በቂ ማብራሪያ ሰጥቼ ነበር፡፡ ሊያስጠይቀኝ የሚችልና ለክስ የሚያበቃ ምንም ጉዳይ እንደሌለ በማስረዳት ተግባብተን ነበር የተለያየነው፡፡

ከዚያ ቀጥሎም፣ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ምንም አይነት የጥያቄም ሆነ የአቋም ለውጥ ሳያደርግ እንደገና በሌላ ሁለተኛ ዙር በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንድሰጥ ጠየቀኝ፡፡ እኔም በተጠየቅኩት መሰረት በቂ ማብራሪያ በመስጠት፣ ሊያስከስሰኝ የሚችል ምንም ጉዳይ እንደሌለ በአሳማኝ ማስረጃዎችና በምክንያታዊነት አስረዳሁ፡፡

ያቀረብኩት ማብራሪያ አሳማኝ ሆኖ ሳለ ግን፣ የመንግስት ፍላጎት በሚመስል እናባልጠበቅኩት መልኩ ወደ እስር ቤት እንድገባ ተደረግኩ፡፡ በዚህ መልኩ በቂ መረጃና ማስረጃ በሌለበት ወህኒ ከተወረወርኩና እስር ቤት ታጉሬ ፍትህ ፍለጋ ቀናትን፣ ሳምንታትንና ወራትን መቁጠር ከጀመርኩ ይሄው ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡

ባለፈው ታህሳስ 17 ቀን 2012 ዓ.ም…

ማልጄ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ስሄድ፣ በእለቱ የሚሰየመው ችሎት የመጨረሻ ብይን እንደሚሰጠኝ በመተማመንና በሙሉ ተስፋ ነበር፡፡ ችሎቱ ሌላ ቀጠሮ ሲሰጥ ግን፣ በውስጤ የተዘራው ተስፋ ድንገት መከነ፡፡ ቀጣይ ያልታወቁ ወራትን በእስር ስማቅቅ እንድገፋ የሚያደርገኝ ቀጠሮ የተሰጠኝ፣ ከፍርድ ቤቶች በስተጀርባ ባሉት ስውር እጆች ግፊት እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ታየኝ፡፡

ይህን እውነታ እየተረዳሁ፣ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ መተማመን ከንቱ ጅልነት ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ከዚህ በኋላ የሚሰጠው ፍትህ ቢኖር እንኳን፣ “የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል” የሚለው ብሒል እንኳን የሚገልጸው አይመስለኝም፡፡

በአገራችን ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን ለመገንባት በተደረገውረጅም ትግል የተከፈለው መስዋዕትነት፣ በጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ በፖሊስና በፍርድ ቤቶች ነውረኛ እና ወጋኝ አካሄድ ከንቱ መቅረቱን ባሰብኩ ጊዜ ጥልቅ ሃዘን ይሰማኛል፡፡

በየዘመናቱ ለመጣው አምባገነን ስርዓት ሁሉ ትልቅ መገልገያ ሆነው የዘለቁት ከላይ የጠቀስኳቸው ተቋማት ነጻና ገለልተኛ መሆን እስካልቻሉ ድረስ፣ የዜጎች መብት ይረጋገጣል ብሎ ማሰብ ፍጹም የማይታሰብ ነው፡፡

የታመመውን የአገራችን ኢኮኖሚ ለማከም እንዲሁም በስርዓቱ ተስፋ ቢስ የሆኑ የአገራችን ወጣቶችን ወደ ዘላቂ መሻሻልና ዕድገት ሊወስዱ የሚያስችሉ ትልልቅ ዕቅዶችን ለመተግበር በተነሳሁበት ወቅት፣ከበስተጀርባ ባሉ ስውር እጆች የሚጎነጎንብኝ ሴራ እና የሚፈጸምብኝ ደባ፣ ፖለቲካዊ ባህሪ እንዳለው ለመገንዘብ ችያለሁ፤ መላው ኢትዮጵያዊም ይህንን እውነታ እንዲረዳልኝ እፈልጋለሁ፡፡

ከአሁን በኋላ ከወገንተኝነት ካልጸዳ ፍርድ ቤት ችሎት መታደም፣ “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” እንደሚሉት ራስን ማታለል ሆኖ አግኝቼዋለሁ፤ ስለሆነም የራሴን አቋም መያዜን እና ከዚህ በኋላ ፍትህ ፍለጋ ወደ ፍርድ ቤት ላለመሄድና ችሎት ፊት ላለመቅረብ ቁርጥ ውሳኔ ላይ መድረሴንለህዝቡ በይፋ ለማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡

በመጨረሻም በኖቤል የሰላም ተሸላሚው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ እንዲሁም በጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ በጠቅላይ አቃቤ ህግ እና በሌሎች ተቋማትና ሃላፊዎቻቸው ላይ የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘንና በእነሱ ተስፋ መቁረጤን ሳልናገር ማለፍ አልፈልግም፡፡

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለመሰረታዊና ለሁለንተናዊ ለውጥ ዝግጁ የሚሆኑበት፤ ዘላቂ ትግል በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን መገንባት የሚያስፈልግበት ጊዜው አሁን ነው!!!

(የማይነበብ ፊርማ)

ኤርሚያስ አመልጋ ፣ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አዲስ አበባ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: ermiyas amelga, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule