• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መዘጋቱ ታቅዶ የተከፈተው የአህያ ቄራ

April 19, 2017 11:31 pm by Editor 1 Comment

በህወሃት ፈቃድ በቢሾፍቱ የተከፈተው አህያ ማረጃ (ቄራ) መዘጋቱ በእንግሊዝኛ የሚታተመው ፎርቹን ጋዜጣ ከሁለት ቀናት በፊት ዘግቧል፡፡ ቄራው የተከፈተ ሰሞን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ድጋፍ እንደነፈገው አብሮ ተዘግቧል፡፡ ቄራው የተከፈተው እንደሚዘጋ ታቅዶ ነበር፡፡

የዛሬ ሦስት ሳምንት አካባቢ በቻይናዊ ባለሃብት ከአዲስ አበባ 48ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማ የአህያ ማረጃ መከፈቱ ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ በብዙዎች ዘንድ የመወያያ ርዕስ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ከውይይቱም ባለፈ በርካታዎች ጉዳዩን ከህወሃት/ኢህአዴግ ባለሥልጣናት ጋር በማገናኘት የመሳለቂያ አጀንዳ አድርገውት ከርመዋል፡፡ መዘጋቱንም በተመለከተ “አንዳንድ ባለሥልጣኖችን ከሥጋት ለመታደግ ነው” በማለት የተሳለቁም አሉ፡፡

ቄራው በሥራ በቆየበት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ሦስት መቶ አህዮችን ማረዱ ፎርቹን መረጃ ያቀበሉትን “ምንጮች” ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ዕቅዱ በቀን 200 አህዮችን ለቢላ በመዳረግ ሌጦውን ወደ ቻይና ሥጋውን ወደ ቪዬትናም ለመላክ ነበር፡፡

በኦሮሚያ አስተዳደር ስም ፈቃዱን የሚሰጠው የህወሃት አገዛዝ ሆኖ ሳለ አሁን ደግሞ ለመዘጋቱ በህወሃት አገዛዝ ሥር ያለው “የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን” ኮሚሽነር “እንዲህ ያለ ኢንቨስትመንት ተቀባይነት የለውም” ማለቱን ፎርቹን ተናግሯል፡፡

“(እኤአ) ከ2014ዓም በፊት ከተመዘገቡት በስተቀር እንዲህ ዓይነት ኢንቨስትመንት ከኅብረተሰቡ ባህልና እሴት ጋር የሚጋጭ ስለሆነ መቀበል አቁመናል” ብሎ ኮሚሽነሩ መናገሩን ፎርቹን ጨምሮ ዘግቧል፡፡

ጋዜጣው ይህንን ከማለቱ ጋር አያይዞ የኮሚሽነሩ ንግግር ከሦስት ሳምንት በፊት ለፎርቹን የተነገረው መሆኑን አክሎ ተናግሯል፡፡

ኮሚሽነሩ ይህንን ማለቱ ከሦስት ሳምንት በፊት እየታወቀ የዕርድ ቦታው ለምን እንደተከፈተ ጋዜጣው ምንም የሰጠው ማብራሪያ የለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከ2014 ጀምሮ ለእንደዚህ ዓይነት የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተከለከለ ከሆነ ቄራው በምን አግባብ በ2017 ሊከፈት እንደቻለ ምንም አልተባለም፡፡ ምናልባት የቄራው ኩባንያ ከ2014 በፊት የተመዘገበ ድርጅት ነው ከተባለ የማይመለከተው “ሕግ” ለምን ተፈጻሚ እንደሆነበት የተሰጠ ማስተባበያ የለም፡፡ ከዚህ ሌላ “የኅብረተሰቡ ባህልና እሴት” ከ2014 በፊት በተመዘገቡ ድርጅቶች ላይ ተፈጻሚ የማይሆንበት አግባብም ግልጽ አልሆነም፡፡ በሌላ አነጋገር ከ2014 በፊት የተመዘገቡ የኢንቨስትመንት ድርጅቶች ከአህያ እስከ አይጥ እያረዱ ሥጋውንና ሌጦውን መሸጥ ይችላሉ ማለት ይመስላል፡፡ የኢትዮጵውያን “ባህልና እሴት” ዕውቅና ያገኘው በ2014 ነው የማለት ያህል ነው የኮሚሽነሩ ንግግር፡፡

ቄራው መከፈቱን የዘገበው ፎርቹን ጋዜጣ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን የኮሚሽነሩን ቃል ያኔውኑ ያገኘው ቢሆንም በወቅቱ ግን አብሮ አልዘገበም፡፡

ከህወሃት የተሰጠውን ተስፋና ቃል የሚያውቀው የቻይና ኩባንያ ጉዳዩን ለዓለምአቀፍ ፍርድቤት አቀርባለሁ ማለቱ የኮሚሽነሩ ቃል ውሃ የማይቋጥር መሆኑን የሚያስረዳ ሆኗል፡፡ እንደ አንድ ዓለምአቀፋዊ የኢንቨስትመንት ኩባንያ ድርጅቱ ቄራውን ከመክፈቱ በፊት የተለያዩ (የአካባቢ፣ የሕግ፣ ወዘተ) የአዋጭነት ጥናቶች (feasibility studies) ሳያደርግ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንደማያፈስ ግልጽ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ፈቃድ ሰጪው ህወሃት ሆኖ ሳለ “የኅብረተሰቡን ባህልና እሴት” የሚቃወም ኢንቨስትመንት ነው በማለት አሁን እንዲዘጋ ማድረጉ እርስበርስ የሚጣረስ ሃሳብ ሆኗል፡፡

ከውጭ ዜጋው በስተቀኝ አቶ ገብረመድኅን አርአያ “ለሸጡት እህል” ገንዘብ ቆጥረው ሲቀበሉ::

ከበረሃ ጀምሮ ለረሃብተኞች የተሰጠ እህል በመስረቅ የሚታወቀው ህወሃት ከቻይናው ኩባንያ ጋር “የውጫሌ” ዓይነት ስምምነት ካልተፈራረመ በስተቀር ቄራው እንዲከፈተም ሆነ ከተከፈተም በኋላ ያለውን “ግለት” አይቶ እንዲዘጋ የወሰነው ህወሃት/ኢህአዴግ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ቄራው የተከፈተው የመዝጊያ ዕቅድ ተደርጎለት ነው ማለት ይቻላል፡፡

የአህያ ማረጃው በተከፈተ ወቅት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ““ኢጂኣኦ” – የቻይናና አህያ ፍቅር – ቻይና በዓመት 4 ሚሊዮን የአህያ ሌጦ ትፈልጋለች” በሚል ርዕስ ያቀረበው ዘገባ ላይ “ህወሃት “የአህያውን ዘመን አልፌዋለሁና አይመለከተኝም” ካላለ” በስተቀር የአህያ ቄራ እንዲከፈት መወሰኑ ከማንነቱ ጋር የማይስማማ ነው፤ “ደሳለኝ” ብለው የሚያቆላምጡት አህያ እንዳልነበራቸው አህያ እንዲጠፋ መቃብሩን ኦሮሚያ ላይ ተከሉ!! ልክ እንደ ሰይጣን ህወሃትም ወዳጅ የለውም!” በማለት ህወሃት ወዳጅ አልባ እንደሆነ ገልጾ መዘገቡ ይታወሳል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ali says

    April 20, 2017 04:55 am at 4:55 am

    Goolgul,
    I always admire the professionalism that you stand on the top of all other Ethiopian Medias. Be it the timeliness of the subject matter that you discuss, the proofreading (no typos, mis-placed punctuation etc…) quality of you publications. It’s almost only your site that I visit whenever I want to read about Ethiopia & Ethiopian-related matters.
    Keep it up.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule