• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰሞኑ “የኦሮምያ ግርግር” ግራ ገብቶኛል

January 7, 2016 05:43 am by Editor 1 Comment

በሁለት ደረጃ የሚቀርቡ ጥያቄዎች አሉኝ፤–

አንድ፡– ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ? ወይስ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?

ሁለት፡– የኢትዮጵያ የመሬት ጉዳይ ኦሮሞዎችን ብቻ የሚመለከት ነው? ወይስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ?

አንደኛ፣ ግልጽ ከሆነው እውነት እንነሣ፤ ኦሮምያ ከኢትዮጵያ አልተለየም፤ ስለዚህም ግርግሩ የኢትዮጵያ ነው እንጂ የኦሮምያ አይደለም፤ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከወያኔ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ቁርጠኛ ትግል ቁርጠኛ ዓለማና ቁርጠኛ ስልት ያስፈልገዋል፤ ስለዚህም ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል፤ የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም፤

ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤

አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤

ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ወያኔዎች ብቻ ናቸው ማለት ነው፤ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡

አደጋው ወደሁለተኛው ጥያቄ ይመራናል፤ ገብቶኝ እንደሆነ የግርግሩ ምክንያት ሁለት ናቸው፤ አንዱ ከቤት-ንብረት መፈናቀል ነው፤ የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ነው፤ ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች ሚደፈጥጡ ናቸው፤ ልብ በሉ የኦሮሞን የዜግነት መብቶች ይደፈጥጣል አላልኩም፤ የኢትዮጵያውያንን ሁሉ መሠረታዊ መብቶች የሚደፈጥጥ ነው፤ ይህ የማያጠራጥር እውነት ነው፤ ይህንን ከተቀበልን ጉዳዩ የኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ግርግሩም የኦሮሞ ብቻ አይደለም፡፡

ትልቁ አደጋ ያሁንን ግርግር የኦሮምያ ብቻ ካደረግነው ወደፊት ያው ጉዳይ በሌሎች ጎሣዎች መሀከል ሊነሣ ነው፤ ሌሎች ግርግሮች ሊያስፈልጉ ነው፡፡

ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ታኅሣሥ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 11, 2016 11:10 pm at 11:10 pm

    አዎን! ግርግሩ ግራ ያጋባል….!?
    (ግርግር ለሥልጣን ያመቻል ግን ጭቆናን ለውጦ ጨቋኝን ያቀያይር እንደሆን እንጂ መፍትሔ አይሆንም።)
    (፩) – ግርግሩ የኦሮምያ ነው? ወይስ የኢትዮጵያ?
    ** ሠልፈኛው ለብቻ!..ፖለቲካ ተንታኙ ለብቻ! ነፃ አውጭው ለብቻ!… ግራ የገባውና ያልገባው ለብቻ!..የገባውና መግቢያ የሚፈልገው ለብቻ! …ሳይገባው ግራ የሚያጋባው ለብቻ! መግለጫው(መላጫው) ለብቻ!ግራ ተጋብቶ የሚያግባበው ለብቻ! ማስፈራሪያና ዛቻ አዘል ፅሑፍ የሚለቀው ለብቻ! አንድንት ኅብርት አሁን በአስቸኳይ ዋ! በኋላ የሚሉና እንደ ኢህአዴግ አስበው እንደ ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኛ ተውነው ብሔራዊ አመፅ የተጠናበረባቸው…. በቋንቋና ብሔር ተኮር በመፈቃቀድና መፈቃቀር በደስታ ኖረው ከፌደራል መንግስት በጉርብትና እንኖራለን እንጂ በፌደራል ሥርዓት አንመራም የሚሉ!?(ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ተለይቷል?) በአትድረሱብንና በድረሱልን መካከል ያለው ውዥንብር፣ይህ በበኩሌ የራስን ድክመት በሌላው ለጥፎ መጯጯህ(የጨረባ ተስካር) በጭራሽ ሊታረምም ሊወገድም ያልቻለ የዓርባ ዓመት አዙሪት ነው።
    ** አንደኛው “የጋኔልና የሰይጣን የጥንቆላና መልክተኛ ሰልፍ” ሲል ሌላው “የቡዳ ፓለቲካ” ሲል ያደምቀዋል። ሕገመንግስቱ ይከበር ሲሉ ይጮሃሉ…ትነአግ/ኢህአዴግ እያስከበርኩ ነው ሲል ሌላው ተነስቶ ተከፋፈልን ተለያየን ይልና ያለቅሳል…ያላቅሳል፡ከተማ ሲስፋፋ ማንነታችን ይጠፋል ባሕልና ቋንቋችን ይበከላል ሲል ይፎክራል! ወዲያው ቋንቋችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ይሁን ያለ ውድድር ምክር ቤቱም ፖለቲካል ኢኮኖሚውም እኛ ካልገባን ቃል የተገባልን ልዩ ጥቅማጥቅማችን ይከበር ይላል ። ‘ልዩነታችን ውበታችን’ ሲባል ሁሉም ይጨፍራል!! ቀጥሎ አንከፋፈልም አናሳ ብሔር በትልቅ ብሔር አይገዛም! ይላል…ይህ የእኛ ያም የእኛ! ‘ሐጎስን’ ንቀለው ‘ቶላን’ ትከለው ሲል ሌላው የእኔ ቱ ነው? የእነሱ የእኔ አደለምን ማለት ነው!? ሲል የተነሱበትን ንፋስ እረስተው ሌላ እሳት ጭረው ቀጠሉ… ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ‘ተከልሎና ተከልክሎ’ የመፈክሩ መልዕክት እንኳ ለጎረቤቱ ሳይገባው ሕፃናት ከፊት አሰልፎ ሕዝባዊ ንቅናቄ በፍልጥ እነጨትና ድንጋይ ወታደሩን መተነፋፋሻ አሳጣው አተረማመሰው!አርበደበደው!(ልክ ተስፋዬ ግበረእባብና ጀዋር ሙድ!)ነፃ አውጭው ምንሊክ ቤተመንግስት ሊቆጣጠር ፳ ኪሜ ቀረው! ታይቶም፣ ተሰምቶም፣ የማይታወቅ አብዮት (እራስን ማድነቅ! )እና መጃጃል። ታዲያማ እነ አጅሬዎችም (ሙስና መሮች፣አድርባዮች፣አውርቶአደሮች፣ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ቤተሰባዊ ደላሎች ስለ ሚ/ሩ ብለው መፈረም አቅም ያላቸው) ይችን ይዘው ጦራቸውን ጭነው ከተፍ አሉ የድሃ ልጅ በባዶ ሆዱ ኢላማ ሆነ ማን ተጠተቀመ?…. “ያልታደለች አፍሳ ለቀመች”
    …” ግርግሩ የኦሮሞ ከተባለ ሁለት ውጤቶች ይከተላሉ፤ አንዱ ውጤት ከኦሮሞ በቀር ሌላውን ሕዝብ አያገባውም ማለት ይሆናል፤ ሁለተኛው ውጤት የልዩነቱ ባለቤቶችና ተፋላሚዎች ኦሮሞዎችና ትነአግ/ ህወአት ብቻ ናቸው ማለት ነው፡ ይህ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡(፩) ከቤት-ንብረት መፈናቀል(፪) የዜግነት መብትና መገለጫ የሆነውን መሬት ማጣት ሁለቱም መሰረታዊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነትን የዜግነት መብቶች የሚደፈጥጡ ናቸው።ግርግሩን የኦሮሞ ብቻ ማድርግ ጥንቱኑ ለማጋጨት የተሰጠውን ስያሜ በስምነቱ ከማጽደቅ በላይ ለታቀደው ዓላማ አመቺ መሣሪያ ማድረግ ነው፤ ይህ ደግሞ በቅድሚያ መሸነፍን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ከትነአግ/ኢህአዴግ በቀር ደጋፊ ያለው አይመስለኝም፤ ጉዳዩ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሆነ ትግሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ መሆኑ ታምኖበት ቁርጠኛ ትግል! ቁርጠኛ ዓለማ! ቁርጠኛ ስልት! ቁርጠኛ መሪ ያስፈልገዋል።አራት ነጥብ።
    **” የሕመሙን መርዝ እየተጎነጩ ከሕመሙ ፈውስ ለማግኘት አይቻልም ሲባል “ሲፈጀኝ በማንኪያ ሳይፈጀኝ በጄ” ዘላቂ ትግልና ዘላቂ አስተማማኝ ለውጥ ማግኘት በጭራሽ አይቻልም። በሁለቱም ጎራ “ልታስጠብብ ሄዳ አሰፍታ መጣች!” እንዳይሆን አደራ! አደራ! ስለ ሀገረ ኢትዮጵያ ሠላም የሚያስቡ ሠላም ይክረሙ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule