• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰላማዊ ሰልፍ መንፈስ መመለስ

March 30, 2014 04:46 am by Editor Leave a Comment

በበርካታ ኢትዮጲያዊያን ትውስታ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ሲባል ወደ አእምሮአቸው የሚመጣው በምርጫ 97 ሰሞን የነበሩት ህዝባዊ የመብት ጥያቄዎች ናቸው። በወቅቱም ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው ከአሁን በውሃላ ማንም ሰው አደለም ተሰልፎ ሰብሰብ ብሎም መቆም አይችልም ብለው ማስጠንቀቂያ በመስጠት ህዝቡን በየእስር ቤቶ ካጎሩት በውሃላ መብትን በሰልፍ የመጠየቅ ነገር በዛ በይስሙላ ህገ መንግስት ላይ ብቻ ተወስኖ በሰልፍ መብትን የማስከበር መንፈስም በእጅጉ ተቀዛቅዞ ነበር።

እንደውም በአንድ ወቅት ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳን ከእስር መፈታት አስመልክቶ ለተጠራው ሰልፍ መንግስት ከሁለት መቶ ሃምሳ ሰው በላይ መሰለፍ አይፈቀድም የሚል ብዙዎችን በግርምት ያስደመመ ተሰምቶ የማያውቅ የሰላማዊ ሰልፍ ፍቃድ አሰጣጥ ሂደትንም አስተውለን ነበር።

ምንም እንኳን በራሱ በወያኔ ህገ መንግስት የዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ቢደነገግም ያው እንደሚታወቀው ህገ መንግስቱን እንዳሻው የሚቀያይረውም ሆነ የሚተረጉመው ራሱ ወያኔ ስለሆነ ለበርካታ አመታት የዜጎች መብትን በሰልፍ የመጠየቅ ነገር የሚያሰቅል ወንጀል ሆኖ ቆይቶ ነገር ግን ከጥቂት ግዜያት ወዲህ በመጠኑም ቢሆን የመመለስ መንፈስ እያሳየ ይገኛል። እሱም ቢሆን ኑሮው ስለከበደ፣ ግፉ ስለበዛ ፣ ህዝቡም አሁንስ የመጣው ይምጣ በማለቱ እንጂ የወያኔ መንግስት ተሻሽሎ ወይም ለውጥ አሳይቶ አይደለም።

ለዚህ የሰላማዊ ሰልፍ መንፈስ መመለስ የሰማያዊ ፓርቲና የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት የሚያስመሰግን ስራን ሰርተዋል። የተቀዛቀዘውን የህዝቡን መብትን የመጠየቅና የማስከበር መንፈስ በማነሳሳትና መብትን የመጠየቅ እሳቤ ክህዝቡ አእምሮ ውስጥ ዳግም እንዲንሰራራ አድርገዋል። እኛም በርቱ በዚህ ቀጥሉ እንላለን። በቅርብ ቀንም ሴት እህቶቻችን “የጣይቱ ልጆች” በተዘጋጀው የሩጫ ውድድር ላይ ወያኔን ያስደነገጠ ፣ የመብት ረገጣን በፅኑ የሚቃወም ፣ የህዝቡንም በመንግስት ባዶ ፕሮፓጋንዳ መሰላቸት የሚያሳይ ፣ መጠኑ ለሰፋው የኑሮ ውድነት የመንግስት የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ ምላሽ እንዲሁም ሌሎች በርካታ ወያኔያዊ ግፎችን በከፍተኛ መልኩ ተቃውመው አስመስጋኝና አርአያ ሊሆን የሚችል ተግባር ፈፅመዋል። የወያኔ መንግስትም እንደተለመደው ሰብስቦ እስር ቤት አጉሯቸዋል።

ሳራ ግርማ
ሳራ ግርማ

እዚህጋ ሁላችንም በአግባቡ ማስተዋል ያለብን ህዝብ መብቱን በሰላማዊ ሰልፍ ለማስከበር ሲጀምር በርካታ ችግሮች ማለትም እስር፣ እንግልት እንዲሁም ከዛም የከፋ ችግር በወያኔ መንግስት አማካኝነት እንደሚፈጠር ነው። ነገር ግን የመብት ጥያቄ ተመልሶ የዜጎች መብት እስኪከበር እንዲሁም በህዝብ የተመረጠ የህዝብ አገልጋይ መንግስት እስኪፈጠር ድረስ የመብት ማስከበር ትግሉ መቀጠል አለበት።

የወቅቱም የሃገራችን በሰላማዊ ሰልፍ መብትን የማስከበር መንፈስ መመለስና መነቃቃት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የፖለቲካ ፓርቲዎችና የፖለቲካ ሰዎች እንዲሁም የዜጎች መብት መከበር ዙሪያ የሚሰሩ አካላት የተጠናከረ አስተዋፅዖ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኑር !!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule