• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መጪው ጊዜ ለናይጄሪያ “ብሩህ” ይሆናል!!

April 4, 2015 04:22 am by Editor 2 Comments

በናይጄሪያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ የፖለቲካ አካሄድ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያመጣል የተባለው የሰሞኑ ምርጫ ውጤት ተሰናባቹን ፕሬዚዳንት የመንፈስ ልዕልና አጎናጽፏቸዋል፡፡ በበርካታ ችግሮች ለተወጠረችው ናይጄሪያ “ብሩህ ጊዜ” ያመጣል ተብሎም ይጠበቃል፡፡

ፕሬዚዳንት ጉድላክ ዮናታን በምክትልነት ናይጄሪያን እያገለገሉ በነበሩበት ጊዜ በወቅቱ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዑማሩ ሙሳ ሕይወታቸው በማለፉ ወዲያው የፕሬዚዳንትነት መንበሩን ተረከቡ፡፡ ዑማሩ ሙሳን ተክተው ጥቂት እንዳገለገሉ በወቅቱ በተካሄደ ምርጫ ሙሐማዱ ቡሃሪን አሸንፈው ናይጄሪያን ለአምስት ዓመታት መርተዋል፡፡ አሁን ደግሞ የዛሬ አምስት ዓመት ባሸነፏቸው መልሰው ተሸንፈው ሥልጣናቸውን በሰላም አስረክበው በናይጄሪያ የምርጫ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ተግባር በመፈጸም ስማቸውን ከመቃብር በላይ ህያው አድርገዋል – ፕሬዚዳንት ጉድላክ ዮናታን!!

ፕሬዚዳንት ዮናታን በሥልጣን በቆዩባቸው ዓመታት በርካታ ተግባራትን እንዳላከናወኑ እንዲያውም ላሁኑ ሽንፈታቸው እነዚሁ ጉዳዮች እንደ ምክንያት ይጠቀሳሉ፡፡ የቦኮ ሃራም፣ የሙስና፣ የኢኮኖሚ አለማደግ፣ ወዘተ አንኳር ጉዳዮች ዮናታንን እንዳይመረጡ እንዳስደረጓቸው በስፋት ከሚነገሩት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

በምርጫው ዘመቻ ወቅት ውጤቱ ምንም ይሁን ግልጽና ፍትሐዊ ምርጫ በናይጄሪያ እንደሚደረግ ቃል የገቡት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጉድላክ ቃላቸውን ጠብቀዋል፤ የተናገሩትን ፈጽመዋል፤ የጀመሩትን ጨርሰዋል፡፡ የመራጩ ሕዝብ ድምጽ ሙሉ በሙሉ ተቆጥሮ ከመጠናቀቁ በፊት መሸነፋቸውን ባመኑበት ጊዜ ባልተጠበቀ ሁኔታ ተቀናቃኛቸውን ጄ/ል ሙሐማዱ ቡሃሪን “እንኳን ደስ አልዎት” በማለት አመስግነዋቸዋል፡፡ ለናይጄሪያ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በሕዝብ በመመረጣቸውም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡ የሕዝብን ድምጽ እንደሚያከብሩ የሰጡትን ቃል በመፈጸም በአገራቸው ታሪክ የማይረሳና የማይሻር አሻራቸውን አትመዋል፡፡ ደም መፋሰስን ገትተዋል፤ ውድመትን፣ ጥላቻን፣ መራርነትን፣ ወዘተ አክሽፈዋል፤ የማያቋርጠውን የሥልጣንና የአምባገነንነትን አዙሪት ሰብረዋል፤ በዚህ ተምሳሌነታቸው እንደ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ እምነት ለሞ ኢብራሒም ፋውንዴሽን ብቻ ሳይሆን ለኖቤልም ብቁ ተሸላሚ ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡

ጉድላክ ዮናታን በአገሪቱ ሚዲያ ባስተላለፉት “ሽንፈትን የመቀበል” መግለጫ ላይ “ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንዲካሄድ ቃል ገብቼ ነበር፤ ቃሌን ጠብቄአለሁ፤ ከዚህ በተጨማሪም ናይጄሪያውያን በዴሞክራሲ ሒደት ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ ምህዳሩን አስፍቼአለሁ፤ ይህ ለአገሬ ትቼ የማልፈው አንዱ ውርስ (ሌጋሲ) ነው፤ ወደፊት እንዲቀጥልም እመኛለሁ” ብለዋል፡፡ ምርጫው ሰላማዊና የተሳካ አንዲሆን የአገሪቱ የደኅንነት ኃይል ላከናወነው ሥራ አድናቆታቸውን ችረዋል፤ የፓርቲ ሰዎቻቸውን እና ዴሞክራሲያዊ መብቱን በተግባር የተጠቀመውን የናይጄሪያን ሕዝብ አመስግነዋል፤ በመጨረሻም ለጄኔራል ሙሃማዱ ቡሃሪ መልካሙን ሁሉ በመመኘት አገራቸውን ፈጣሪ እንዲባርካት በመማጸን ንግግራቸውን አጠናቀዋል፡፡

ሙሃማዱ ቡሃሪ ከጉድላክ ዮናታን የመልካም ምኞት መልክት ሲቀበሉ
ሙሃማዱ ቡሃሪ ከጉድላክ ዮናታን የመልካም ምኞት መልክት ሲቀበሉ

በአገራችን ይካሄዳል ተብሎ ከሚጠበቀው ምርጫ አኳያ የናይጄሪያው አስቀድሞ መከሰቱ፤ ውጤቱ ያልተጠበቀ መሆኑ እንዲሁም የሥልጣን ሽግግሩ “በመተካካት” ሳይሆን በሕዝብ ምርጫ መከናወኑ የበርካታዎችን ቀልብ የሳበ ሆኗል፡፡ በተለይም በናይጄሪያ ታሪክ በሥልጣን ላይ ያለ ፕሬዚዳንት በምርጫ ተሸንፎ ከሥልጣን ሲለቅ ይህ የመጀመሪያው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ገዢዎቿ ካልተፈነቀሉ ወይም ካልሞቱ ወይም ካልተሰደዱ መሪ ለመለወጥ ታድላ የማታውቀው አገራቸው ለዚህ ዕድል የምትበቃበት ዘመን መቼ እንደሚሆን የሚጠይቁና የሚወያዩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡

ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሚወዳደሩበት አካባቢ ለጎልጉል የተላከው መልዕክት እንዲህ ይላል፤ “በመጪው ምርጫ ብዙ አንጠብቅም፤ ሃይለማርያምም “ውርስ ተቀባይና አስፈጻሚ” እንደመሆናቸው ብዙ ይከውናሉ ብለን አንጠብቅም፤ ቢያንስ ግን እርሳቸው በሚወዳደሩበት ቦታ ፍትሓዊ የምርጫ ውድድር እንዲኖር በማድረግ ለፓርቲያቸው ሳይሆን ከፓርቲቸው በላይ ለሆነው ሃይማኖታቸውና ለሚያመልኩት አምላክ ታማኝ ቢሆኑ ይበቃናል”፡፡

ጉድላክ ዮናታን በወሰዱት እርምጃ “ከአፍሪካ መልካም ነገር አይወጣም” ለሚሉት ምዕራባውያን የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆነዋል፤ በርካታዎችን አስገርመዋል፤ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት መሪዎች “የጀመሩትን መጨረስ” ምን ማለት እንደሆነ በተግባር አሳይተዋል፤ በተለይ “ምርጫ” ለማድረግ ደፋ ቀና ለሚሉ ምን ዓይነት መንገድ መከተል እንደሚገባቸው ሽንፈትን በመቀበል እንዴት አሸናፊ መሆን እንደሚቻል መስክረዋል፤ ለአገራቸው መጪው ዘመን “ብሩህ” እንዲሆን ታላቅ ተስፋ ፈንጥቀዋል፡፡ መልካም ዕድል (ጉድላክ) ዮናታን!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    April 4, 2015 11:37 am at 11:37 am

    አዎን! ይችን አጋጣሚ ስንት ሰው ጓጉቶላት ነበር!?ብጥብጥ ቢነሳ እጀ-እረጃጅሞች የት እንደሚደርሱ..አጫጭሮች ማን ትከሻ ላይ ፊጥ ብለው እንደሚታዩ.. የማይታዩ፣ የማይዳሰ፣ሱ የማይጨበጡ፣ ሕዝብን ቀውጠው እንዴት ሳይነግዱ እንደሚያተርፉ…ያለው የሌለውን እንዴት እንደሚሸፍን..የሌለው ያለውን እንዴት አንደሚቦጭቅ…በዚች ግርግር ሀገርና የህዝብ ሀብት እንዴት እንደሚባነን…ማስረጃና መረጃ እንዴት እንደሚጠፋ ያለሙ፣ ያቀዱ፣ ያሰቡና ያሳሰቡ..ያሰፈሰፉ የውስጥም የውጭም ጃርቶች ውጥን እንዲህ በድምፅ ሲመክን መልካም ነው።

    **”ነዳጅ አምራች በሚባሉ ሀገራት ክብሪት በነፃ ይታደላል” ናይጄሪያ በሕዝብ ብዛትም ይሁን በሀገሪቱ ቆዳ ስፋት፣ ባላት ፎቅና መንገድ እርዝመት ሳይሆን ህዝቦቿ ፷ በመቶ ከድህነት ወለል በታች ያሉ ናቸው። አንድ መንግስት ሕዝቡን አስርቦ ለውጥ ሳያመጣ በሥልጣን ላይ የተቀመጠበትን ዘመን በመቁጠር የሕዝብ አበሳን አስቆጥሮ፣ ጥቂቶችን ገንዘብ አብዛኛውን ቂም አስቋጥሮ፣ መጪውን ትውልድ የብድር ዕዳ አቁፋዳ አሸክሞ፣ የሚገሰግስ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሙስና መር ኢኮኖሚ ዕድገትና ግስጋሴ ከአፍሪካ አንደኛ! ከዓላም ሁለተኛ! የሚሉ ቧልት፣ ፌዝ፣ ሽሙጥ፣ ሲሾመጥጥ ጥሩ አይሆንም!? ይህን ያገናዘበው የናይጄሪያ ምርጫ አሳታፊ፣ ፍትሃዊ፣ የሠላም የሥልጣን እርክክብ ትልቁን ክብርና ሞገስ ሊቸረው የሚገባው በሀብት በወታደሩ ብዛት ያልተመካውን በሕዝብ ደምፅ ያመነውን…ጉድላክ ዮናታን…እንኳን ደስ አለዎ አሸንፈዋል!።
    *** ለሀገራቸውና ሕዝባቸው መልካምን በማሰብ ተፎካካሪያቸውን ግባና ሞክረው ‘ጉድላክ’ ማለታቸው የአሸናፊ ታሪክ አስተላላፊነታቸው በቀሪው ዘመናቸው የጠቀለሉትን ሁሉ ሳይጠቀለሉ ፈተው በማስረከባቸው ‘ዮናታንን ጉድላክ ብለናቸዋል…”መለስ ዜናዊን ነፍስ ይማር! ኅይለመለስን ቀስ ብሎ ያብርር! ከኢህአዴግ መንፈሳዊ ቅናተኛ ይችን ተግባር ነጥብ ሳይቀር እንዳለ ቃልበቃል ይኮርጅና ያሳየን….ሠላም ለሁሉም በቸር ይግጠመን

    Reply
    • pheniel says

      April 21, 2015 04:22 pm at 4:22 pm

      ስለ ቦኮሀሬ በደንብ ቢፃፍ?

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule