• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሁለቱም ባዶዎች ነበሩ!”

November 10, 2013 07:53 pm by Editor Leave a Comment

እ’ስራና  ቅል …
አፈጣጠራቸው፣  ቢሆንም  ለየቅል፤
እንደ  አቅማቸው፣  ሠርተው
በሀሳብ – ተግባር፣ ተግባብተው፤
ሰላም አግኝተው፣ አንድነት
ይኖሩ ነበር፣ በአንድ ቤት።

በፍቅራቸው፣ የሚቀናው
ዱባ ግን፣ ጉረቤታቸው፤
ያሴር ነበር ሴራ፣ የሚያሥር
ይሸርብ ነበር ነገር፣ የሚያደናግር፤
ያጠምድ ነበር፣ ወጥመድ
ባረፉበት ቤት፣ ሳይቀር በመንገድ።

እ’ሰራን ሲያገኘው፣ ብሎ  ጎንበስ – ቀና
የሰላምታ አይነት፣ ያዥጎደጉድና፤
በማር የተቀባ፣ የመርዝ ቃላት
ይነግረው ነበረ፣ መስሎ ተቆርቅሪ፣ ለሱ ያዘነለት።

ቅልንም ሲያገኘው ወይም ቤቱ ሄዶ
ከአስረደው በኋላ፣ እንደሚፈልግው በፍቅሩ ተገዶ፤
ምክር ነው እያለ፣ ነገር ይነግረዋል
በማያውቀው ጉዳይ፣ ደሙን ያፈለዋል።

ከለ’ታት አንድ ቀን፣ ሥራ በፈቱበት
በነገር ተይዘው፣ ”በተሰለቡበት”፤
እ’ስራ ተክዞ፣ ወደ ቤት ሲሄድ
ቅልም በበኩሉ፣ ሲያስብ በምንገድ፤
ዓይን – ለዓይን ተጋጩ፣ እጅግ ተፋጠጡ
በሰላምታ ፋንታ፣ ንትርክ መረጡ።

ቅል ኮራ ብሎ፣ ምላሱና ሳለና
ዱባ ከነገረው፣ ብዙ አስታወሰና፤
”እኔ ከ’ንተ አላንስም፣ እንዲያው ባልበልጥህ ”
በማለት ጀመረ፣ “አንተ እ’ስራ ሆድ ነህ!”።
“ለሰው ልጅ አገልጋይ፣ ወሃ ለመያዝ፣ ተመራጭ እኔ ነኝ
እንደ አስፈለጋቸው፣ የሚሽከረክሩኝ።”
”እኔ ቅል ብቻ ነኝ፣ ቶሎ ውሃ በመሙላት የሚመርጠኝ ሰው
ይዘውኝ ቢዞሩ፣ የማልከብዳቸው፣ የምመቻቸው።”

ነገሩ ተካሮ፣ ዱላ መረጡና
ይጣለዙ ጀመር፣ በሰፊው ጎዳና።
ገላጋይ መስለው፣ የቀረቡት ሁሉ
ዘወር ብለው ሄዱ፣ ዱላ እያቀበሉ።
እነሱም ቀጠሉ፣ ቀጠሉ….  ቀጠሉ
እስቲ  እናስብበት፣ ለነገም አላሉ
ጎዳናውን አልፈው፣ ሜዳውንም  ሞሉ።
የመደባደቡ፣ ኃይል ቢያጥራቸው
ተያይዘው ወደቁ፣ ‘ርስ – በ’ርሳቸው
ብትንትንም አሉ፣ መሬት ብትነካቸው።

የእ’ስራና ቅል፣ ዱባ ጉረቤት
ጠቡን ሲከታተል፣ ቁጭ ብሎ በ’ርቀት፤
”ከቶ ማን ያሸንፍ፣ ፈሪ ማን ይሆን”
እያለ ሲደሰት፣ በማየት ፍልሚያውን፤
ወድቀው፣ ተበታትነው፣ ተፈረካክሰው
ሜዳውን ሞልተውት፣ ሲያስታውላቸው
”ለካስ ሁለቱም ባዶዎች ነበሩ!” በማለት ሳቀና
ቤታቸውን ሊወርስ፣ ሄደ እየተዝናና።
—–//——-
ፊልጶስ / 2006  / E-mail: philiposmw@gmail.com
*”ለካስ ሁለቱም ባዶዎች ነበሩ!” የሚለውን የወሰድኩት ከኮንፊሽዬስ አባባል ነው::

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule