• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አህያውን ትቶ ዳውላውን

June 14, 2014 06:31 am by Editor 1 Comment

በአሁኑ ሰዓት በአብዛኛዎቹ ኢትዮጵያዊ የዜና መለዋወጫ መስኮች፤ “ትግሬዎች በዚህ መንግሥት ተጠቅመዋል? ወይንስ አልተጠቀሙም?” የሚለው ጉዳይ ዓይነታ መወያያ ሆኖ፤ መድረኮቹን ሁሉ አጣቦ ይዟል። በመጀመሪያ ደረጃ፤ አንድን ጉዳይ ኢትዮጵያዊ ታጋዮች ሲያነሱ፤ ከትግሉ ዋና ግብ አንጻር ነው። እንዲያው ለወግ ያህል ወይንም ቁጭትን ለመዘርገፍ የሚደረግ ውይይት፤ የታጋዮችን ቀልብ አይስብም። ይኼ ጉዳይ በትግሉ ሂደት ውስጥ ለኢትዮጵያዊ ታጋዮች ምን ይጠቅማል? ትግሉን ወደፊት ከመግፋትና ከግቡ ከማድረስ አኳያ ምን አስተዋፅዖ አለው? ይኼ ወሳኝ ነው።

ትግል በመርኅ የሚካሄድ እንጂ፤ በየተመቸው የሚነዳ መንፈስ አይደለም። በትግሬዎችና ራሱን “የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር” ብሎ በተነሳው ድርጅት መካከል ትልቅ ልዩነት አለ። በእርግጥ የዚህ ግንባር አባላት በሙሉ ትግሬዎች ናቸው። ይኼ በግልፅ ያለና የማያጠያይቅ ነው። ደጋፊዎቹም በአብዛኛው ከዚሁ ወገን መሆናቸው አያስገርምም። ነገር ግን በአማራው ላይ አማራ ነህ ተብሎ መጠቃቱን እያወገዝኩ፤ አኝዋኩ በአኝዋክነቱ መጠቃቱን እያወገዝኩ፤ ትግሬው በትግሬነቱ እንዲጠቃ ሲዘጋጅ ዝም ብዬ የማይበት ዓይን የለኝም። ትግሬውን እንደ አማራው፣ እንደ ኦሮሞው፣ እንደ አኙዋኩ፣ እንደ ሲዳማው፣ እንደ ኦጋዴኑ ልቆምለት ካልቻልኩ፤ ኢትዮጵያዊ ነኝ ማለቴ ውሸታም ያሰኘኛል።

ይህን የማራምደው ትግሬዎችን ወደ ትግሉ ሠፈር ለማምጣት ካለኝ ምኞት አይደለም። አንድ ትግሬም ሆነ አማራ፤ ኦሮሞም ሆነ አኙዋክ፤ ወደ ትግሉ የሚመጣው፤ የትግሉን መርኅ ስላመነበት እንጂ፤ የግል ጥቅም አገኛለሁ ብሎ አይደለም። እንዲህ ያለው፤ ካለበት ቢቆይ ጥቅሙ የበለጠ ይጠበቅለታል። እኔ ይኼን የማራምደው፤ በትግሬዎች ወገን የሚጠቃ የትግሬ ዘመድ ስላለኝ አይደለም። ይኼን የማራምደው የግል ጥቅም የማገኝበት መንገድ ስላለኝ አይደለም። ይኼን የማራምደው ስለማምንበትና ትክክለኛ መርኄ ሰለሆነ ነው፤ ኢትዮጵያዊነቴ ስለሚያስገድደኝ ነው፤ ታጋይነቴ ስለሚያስገድደኝ ነው።

መረዳት ያለብን፤ ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት ለሥልጣን መያዣና አሁንም የሥልጣኑ ማራዘሚያ አድርጎ የያዘው፤ አማራውን በአማራነቱ በማጥቃት ነው። ለአማራው ማጥቂይ አድርጎ ያቀረበው ደግሞ፤ አማራው ተጠቃሚ ነበር፣ አማራው የሥልጣን ባለቤት ነበር፣ አማራው ገዝቶናል፣ በማለት ነው። ይህ ደግሞ መሠረታዊ የሆነውን ኢትዮጵያዊያን ከ፲ ፱ ፻ ፷ዎቹ ተማሪዎች ጀምረው የተነሱለትን በጨቋኝና በተጨቋኝ፤ በገዥዎችና በተገዥዎች መካከል የነበረውን እንቅስቃሴ በመጥለፍ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የአማራው ወገን ሌሎችን በመግዛቱ ነው የሚል የፖለቲካ ስልት በማርቀቅ፤ አነስተኛው ክፍል ብዙኀንን የሚገዛበት ቀመር በማጠንጠን ነው።

እየገዛን ያለው ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት ነው። ትግሬዎች ተጠቃሚ ናቸው፣ ትግሬዎች ገዙን፤ የሚለው እምነት፤ ጠንከኛ ነው። የዚህን መንግሥት የፖለቲካ ተግባር ትክክል አይደለም የሚል የረጋ አእምሮ ያለው ሰው፤ ዛሬ በተገላቢጦሽ፤ ትግሬዎችን በአማራዎች ተክቶ በትግሬዎች ላይ ዘመቻ ማድረግ፤ አንድም የዚህን ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት የፖለቲካ ፍልስፍናና የአስተዳደር መመሪያ እንዲቀጥል ማራገብ ነው፤ ከዚህ ወዲያ ደግሞ እንደዚሁ ወገንተኛ ወራሪ ግንባር የራስን ወገን ለማሰባሰብ የተወረወረ ዘዴ ነው። በሁለቱም በኩል አፍራሽና የኢትዮጵያዊነት ጠር ነው። ይህ ማለት ለዚሁ መንግሥት ያደሩ አልተጠቀሙም ማለት አይደለም። ሆዳቸውን ያመለኩ ግለሰቦች፤ ለዚህ መንግሥት ስግደው ያደሩ ተጠቅመዋል። ከሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች አቧራቸውን ተሸካሚም ሆነውም ለዚህ የትራፊ ለቃሚዎች አሉ። እኒህም ተጠቃሚዎች ናቸው። ከነዚህ ሆድ አደሮች የትግሬነት ደም ጠብታ በሰውነታቸው ቢፈለግ አይገኝም። ስለዚህ፤ የስርዓቱ ደጋፊና ስርዓቱን የሚቃወሙ በሚል ብቻ ነው፤ ኢትዮጵያዊያንን ታጋዮች ኅብረተሰቡን የሚከፋፍሉ፤ ድሮም ሆነ ዛሬ። እዚህ ላይ ተጋዮች የሚለውን አሰምርበታለሁ።

የፖለቲካ አመለካከትንና ተግባርን በዘር ላይ የተመሠረ አድርጎ መመልከት ዘረኝነት ነው። በገዥው ክፍልም ሆነ በታጋዩ ክፍል፤ የፖለቲካ አመለካከትን ከግለሰብ አውጥቶ ከአንድ የኅብረተሰብ ክፍል ጋር ማቆራኘት ስህተት ነው። ይህ አጥር የሌለበት ጉዳይ ነው። ለዚህኛው ይሠራል ለዚያኛው አይሠራም ልንል አንችልም። የወደፊቷ ኢትዮጵያ የሁላችን ኢትዮጵያዊያን እንጂ፤ አንዱን ክፍል የሚጠቅም ወይንም የሚጎዳ መሆን የለበትም። ዛሬ በአማራዋ ላይ እየተፈጸመ ያለው ነገ በትግሬዋ ላይ እንዲደገም አንፈልግም። እናም መላ ኢትዮጵያዊያን፤ ትግሬዎችን ሆኑ ሌሎቹ በዚህ መንግሥት ላይ በአንድነት መነሳት አለብን። የፖለቲካ አመለካከታችን በግለሰብ እንጂ የትውልድ ሐረግ በመምዘዝ መሆን የለበትም።

የኢትዮጵያዊያን ጠላት ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት እንጂ፤ ተጠቀመም አልተጠቀመም፤ የትግራይ ወገናችን አይደለም። ኢትዮጵያ ስንል በወርድና ስፋቷ የሚኖረውን ህዝብ በሙሉ እንጂ፤ አንዱን ክልል ለይተን ነው አይደለም ልንል አንችልም። የፖለቲካ ቁማር መጫወት ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት ባህርይ እንጂ፤ የታጋዮች ባህርይ አይደለም። አውቀውትም ሆነ ሳያውቁት ዛሬ ትግሬዎችን ራሱን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብሎ የሚጠራው መንግሥት ሙሉ ደጋፊ ናቸው ወይንም በዚህ መንግሥት ምክንያት ተጠቃሚ ናቸው ብሎ እንደ አጀንዳ ማራገብ፤ የዚሁ መንግሥት መጠቀሚያ ከመሆን አያልፍም። ከዚያ ካለፈ ደግሞ፤ የራስን ወገን ለይቶ ነፃ አውጪ ግንባር ለማቋቋም መንገድ የማዘጋጃ ሩጫ ነው። ይህ መንግሥት ሊወድቅ የሚችለው ኢትዮጵያዊያን በአንድነት ተነስተን፤ ኢትዮጵያዊያን ነን ብለን ስንቆም ነው። ከዚህ የተለዬ መንገድ፤ የዚህ መንግሥት መጠቀሚያ መሆን ነው።

አንዱ ዓለም ተፈራ፤ የእስከመቼ አዘጋጅ፤

eske.meche@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. RESOM says

    June 30, 2014 11:17 am at 11:17 am

    በእዉነት ከሆነ በዉስታችን ያለዉ ተንኮል ትተን መትፎነት ትተን በመልካምነት ብንመለከት ያለዉ ገዢዉ{መንግስት}ትግሬ ብቻ እንዳልሆነ ልቦናች ያዉቃል ኢትዬ በሙሉ ደማችን በመርዝ አንመርዘዉ አፋችን በቆሻሻ አንሙላዉ እግራችን ወደ ሲሆል አንምራዉ ከመልካም እትፍ ደስታ ከተኮል ደሞ እትፍ…………………….ይገናል ስለዚህ ወገኔ አንሳሳት አንቾክል ከመወሰናችን በፊት እናስብ እ/ር ሆይ የሚያስተዉል አይምሮ ስተን አሜን አሜን አሜን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule