• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚፈራው መጣ!!

August 5, 2013 09:14 am by Editor 3 Comments

ኢትዮጵያችን ታማለች። ኢትዮጵያችን ተወጣጥራለች። ኢትዮጵያችን በአደገኛ መርዝ ተበክላለች። ኢትዮጵያችን ውስጧ ነፍሯል። ኢትዮጵያችን እየቃተተች ነው። ቆዳዋ ሳስቷል። የሚሰማትና የሚደርስላት ስላጣች የያዘችውን ይዛ ልትነጉድ ከጫፍ ላይ ነች። እናም ቅድሚያ ለመቀመጫ፤ ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ!! ማጣፊያው ሳያጥር ሁሉም መንገዱን ይመርምር!!

ኢትዮጵያ በጭንቀት ጣር ውስጥ ስለመገኘቷ ማብራሪያ የሚጠይቁ ዜጎች ያሉ አይመስለንም። ምናልባት ሳያውቁ እየተፈረደባቸው ያሉ ህጻናት ካልሆኑ በስተቀር፤ ችግር ፈጣሪውም፣ የችግሩ ሁሉ ሰላባ የሆነው ህዝብ፤ ሁሉም ከበቂ በላይ መረጃ አላቸው። ኢትዮጵያ ህመሟ ወደ “ሚድን ካንሰርነት” መቀየር የሚችል ስለመሆኑ ዜጎች ያለ “ሰበር ዜና” ይረዱታል።

የሚድን ስንል በቀላል አገላለጽ ችግር ፈጣሪው ኢህአዴግ፣ የኢህአዴግ ሾፌር ህወሃት፣ የህወሃት አገልጋዮች፣ በህወሃት የበላይነት ከበሮ የሚደልቁ ወንድምና እህቶች፣ ጊዜ የሚያረጅና እራፊ ሆኖ የሚያልፍ የማይመስላቸው የትዕቢት ውጤቶች፣ ይህንን ሁሉ ታግለን “ዴሞክራሲ እናወርዳለን” የሚሉ ወገኖች በልዩነት “አንድ” በመሆን ኢትዮጵያን ለህዝብ ውሳኔ አሳልፈው መስጠት ሲችሉ ነው።

“የጦርነት አባቱ እኔ ነኝ፣ እኔ ከሌለሁ አገር ትከስማለች፣ ኢትዮጵያ በደም ትታጠባለች፣ እኔ ወደ ሰሜን እሸሻለሁ … ” እያለ የቀን ቅዠት ቃዥቶ እወክላቸዋለሁ የሚላቸውን ወገኖች በስጋት ጤና እየነሳ ያለው ኢህአዴግ፣ በተለይም ህወሃት ቀን በጨመረ ቁጥር በእሳት እየተጫወተ ነውና የራሱ ደጋፊዎች ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጣ ሊያስገድዱት ይገባል።

የተናፈናቀሉ፣ ከስራ የተባረሩ፣ በቂም ከነቤተሰቦቻቸው ለልመና የታደረጉ፣ ቤተሰቦቻቸው የታሰሩባቸው፣ የተገደሉባቸው፣ በዘራቸው ሳቢያ የመከራ አረም እንዲመገቡ የተደረጉ፣ የተዘረፉና እየተዘረፉ ያሉ ዜጎች፣ በብሄር እየተተመኑ ከተወዳዳሪነት የተገለሉ ኢትዮጵያዊያኖች፣ እምነታችን ተነካብን የሚሉ የኢትዮጵያ ቤተሰቦች … ብዙ ማለት ይቻላል፤ ሁሉም አምርረዋል። ቁጣቸው ከጫፍ ደርሷል። ደጋግመን እንደምንለው ዛሬ ጊዜው የእርቅና ሰላም የማውረድ በመሆኑ ለሚሰሙ ወገኖች “ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ” የሚል አደራ እናስተላልፋለን። በተለይ በ1997 የምርጫ ወቅት ኢትዮጵያን ወደተሻለ ቦታ ሊያደርሳት የሚችለውን ወርቃማ ዕድል ከእጁ እንዲያፈተልክ ያደረገው ኢህአዴግ አሁንም ይህንን ወቅት ጊዜው ሳያልፍና ሁኔታዎች ወደነበሩበት የማይመለሱበት ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ሊጠቀምበት ይገባል፡፡ አገር ካለፈች በኋላ ልማት፣ ህዳሴ፣ ውዳሴ፣ ግድብ፣ … አንዳቸውም አይኖሩም!

አንድ ዓመት ያስቆጠረው የሙስሊሞች ጥያቄ በወጉ ካልተያዘ መከራው እንደሚሰፋ አስቀድመን ለፍልፈናል። ከቀን ወደ ቀን እየገፋ የሄደው ተቃውሞ በወጉ ተመርምሮ እናታችን ኢትዮጵያን ለአደጋ በማይጥል መልኩ እልባት እንዲሰጠው አሁንም ደግምን ደጋግመን እናሳስባለን። በግርግር ሳይሆን በማስተዋል “ቅድመ ሁኔታ” ያስቀመጠ የሰላም መንገድ እንዲፈለግ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲጀምሩ በቀጣዩ ትውልድ ስም እንጠይቃለን። የ“ድምጻችን ይሰማ” ጥያቄ ድምጽ የማሰማትና የመብት ጥያቄ እስከሆነ በአግባቡ ይመለስ፡፡ ከዚህ ሌላ ጥያቄ ካላቸው ለህዝብ ይፋ ያድርጉ፡፡ የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ከኢህአዴግ ጋር ላለፉት ሁለት አሥርተ ዓመታት ሰላማዊ ግንኙነት እንደነበረው ግልጽ ነው – ባለፉት ሥርዓቶች ባልታየ መልኩ በተለያዩ ከተሞች የበርካታ መስጊዶች መሠራትም ሆነ የአምልኮ ሥርዓታቸው መከበር ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ታዲያ አሁን የሃይማኖትና የመብት ይከበር ጥያቄያቸው የሥልጣንና ፖለቲካዊ ይዘት ያለው መስሎ ለምን ቀረበ? እስካሁንስ ለምን መፍትሔ ሊገኝለት አልችል አለ?

የሚፈሩና የሚከበሩ የፖለቲካ መሪዎች የሉንም። የምንወዳቸውና ሲናገሩ የምናዳምጣቸው የሃይማኖት መሪዎች ባለቤት መሆን አልቻልንም። ለተግሳጽ አደባባይ የሚወጣ ሽማግሌ የለንም። ከውጪም ከውስጥም  መተማመን ጠፍቷል። የክስረታችን ብዛት ባዶ አስቀርቶናል። የቀረን አንድ ነገር ቢኖር እማማችን ኢትዮጵያ፣ እያቃተተች ያለችው አገራችን ናት። ይህችኑ ቤታችንን ተረባርበን ማዳን ካልቻልን ሁሉም ያከትምና ላናገግም እናዝናለን። በርካታ ንጹሃንን እናጣለን!! እባክችሁ የህወሃት ሰዎች ሁሉንም ጎን እዩት። ወደ ልባችሁ በመመለስ የእርቅን መንገድ ፈልጉ። በውል እንደምትረዱት ነገሮች ሁሉ መልካቸውን የሚቀይሩበት ወቅት ተቃርቧል። እባካችሁን የኢህአዴግ ሰዎች ያለፍርሃቻ እርቅ በቤታችሁ እንዲታወጅ መስዋዕት ሁኑ። ዝምታችሁን ቅበሩና ኢትዮጵያንና ወገኖቻችሁን፣ ልጆቻችሁን፣ ቤተሰቦቻችሁን አድኑ። የህዝብን ጥያቄ መልሱ!

በወጪ አገርም ሆነ በአገር ቤት የምትኖሩ የእርቅ ሃሳብ ባሪያዎች፣ ኢትዮጵያን ለመታደግ የምትፈልጉ ወገኖች ኢትዮጵያ ላይ ከየአቅጣጫው የተረጨውን የጥላቻ መርዝ ለመግፈፍ ተነሱ። ኢትዮጵያን ለማዳን ይሉኝታና ማመንታት ዋጋ የላቸውምና ከተጋረዳችሁበት መጋረጃ ውጡ። የሃይማኖት አባቶች እባካችሁን ንስሃ በመግባትና ህዝቡንም ንስሃ በማስገባት የሰላም አባት ሁኑ። ቀሪ ዘመናችሁን በደስታ ሰክራችሁ ትኖሩ ዘንድ ያጎደፋችሁትን ስማችሁን አድሱ። አገር ከሌለ መብትም ሆነ ዴሞክራሲ፣ ነጻነት አይኖሩም፡፡ አገር ከሌለ ድምጽ አሰሚም ሆነ ድምጽ ሰሚ የለም፡፡ አገር ከሌለ ልማትና ብልጽግና አለመኖር ብቻ ሳይሆን ተደረገ የተባለውም ወዳለመኖር ይቀየራል፤ አገር ከሌለ ማንነት ይቀራል፤ ይህንን ማስጠንቀቅና የዕርቅ ሃሳብ ማቅረብ ዕልቂት ናፋቂነት አይደለም።

ልብ ያለው ያስተውል! ጆሮ ያለው ይስማ! ኢትዮጵያ እየቃተተች ነው። ማጣፊያው ሳያጥር ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡ (ፎቶ ከፌስቡክ የተገኘ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. አስቴር says

    August 5, 2013 09:20 pm at 9:20 pm

    ርዕሰ አንቀጻችሁን ወድጃለሁ። ይህንኑ የመሰለ አበራ ልኮልኛል። እዚህ ላይ ተጫኑ። በርቱ።
    http://www.ethiopianchurch.org/editorial2/174-%E1%89%A3%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8C%88%E1%89%A3-%E1%8B%90%E1%8B%AD%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%8B%88%E1%8C%A3.html

    Reply
  2. Mesfin says

    August 15, 2013 06:58 pm at 6:58 pm

    I have the premonition such disaster will happen to Ethiopia and its people. However, most of us have not yet wake up and foresee the danger. You have tried to show to everybody of what kind of disaster is looming towards Ethiopia and Ethiopians. As you have said it if we do not react soon we will perish.

    Reply
  3. abraham says

    January 3, 2014 03:15 pm at 3:15 pm

    ኢትዮጵያ አንተ እንደምትመኝዉ ሳይሆን ከደርግ ሰዉ በላዉ ስርአት ወጥታ ለእድገት የምትራወጥበት ጊዜ ነዉ ያለችዉ ምናልባት ጥያቄህ የስልጣን ከሆነ ካንተዉ ጋር ነኝ ግልጹን ከመናገር ይልቅ እንደ አንድ እዉነታ የሌለዉ ዋሾ መቀባጠር ትርፉ ከትዝብት አያልፍም
    ኢትዮጵያን የሚወድ ሁሉ ለሃገሪቱ ጥቂትም ቢሆን ያበረከተ ሊመሰገን ይገባል አለዚያ በዚህ ባለንበት የዉሸት ዘመን ፎልት ፋይንደር መሆን አገሪቷን ተጠቃሚ ከማድረግ ይልቅ ለጉዳት መዳረግ ነዉ ኢትዮጵያ ስሟ እየተለወጠና ባላት አቅም እያደገች ነዉ ሆኖም ምን ያደርጋል ኢሃዴግ ሆነ እንጂ የሚለዉንስ ምን ትለዋለህ አገር በዚህ መልኩ ከድህነት ትወጣለች ብሎ መጠበቅ አይቻልም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule