• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦባማ “የዕረፍት ጊዜ ለማሳለፍ” ወደ ኢትዮጵያ ይጓዛሉ

June 20, 2015 06:52 am by Editor 2 Comments

ዳግም የመመረጥ ጭንቀት በማይኖርበት በሁለተኛው የአስተዳደር ዘመን ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደታየው የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች አፍሪካን ለዕረፍት ይጎበኛሉ፤ ይዝናናሉ፡፡ የዱር እንስሳትን ያያሉ፤ “የአገራቸውን ባህል ልብስ” ከለበሱ የአፍሪካ ሹመኞች ጋር ጥሩ ፎቶዎችን ይነሳሉ፤ የሥልጣን ዘመናቸው ካለቀ በኋላ ለሚመሠርቱት ቤተመጻህፍት ማስዋቢያ የሚሆን ለየት ያሉ ፎቶዎችን ይሰበስባሉ፡፡

መጪው ወር (July) መገባደጃ አካባቢ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለአራተኛ ጊዜ አፍሪካን እንደሚጎበኙ ቤተመንግሥታቸው አስታውቋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ በሚካሄድባት አዲስ አበባ ላይ በመገኘት ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የአባታቸው አገር ነው የሚባለውን ኬኒያ ለመጎብኘት አስቀድመው ዕቅድ የያዙት ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ የመምጣታቸው ጉዳይ አርብ ይፋ መደረጉ አስቀድሞ የታሰበ ሳይሆን እግረመንገድ የተወሰነ ጉዳይ እንደሆነ አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡ በአዲስ አበባው ቆይታቸው ከኢህአዴግ ሹመኞችና ከሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ጋር ይገናኛሉ፤ በንግድ ዙሪያም ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አስቀድሞ ወደ ኬኒያ ሊያደርጉ የወሰኑትን ጉብኝት የተቃወሙት የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች አሁን ደግሞ ኢትዮጵያ በመጨመሯ ተቃውሟቸውን የበለጠ እንዲሰማ እያደረጉ ነው፡፡ ከዓመታት በፊት በኬኒያ ምርጫን ተከትሎ በተነሳው የዘር ዕልቂት እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩት የኬኒያው ፕሬዚዳንት ዑሁሩ ኬኒያታ ጉዳይ መጨረሻው ሳይታወቅ ኦባማ ኬኒያን አይጎበኙም ሲባል መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት በቂ ማስረጃ በማጣቱና ኬኒያም ለመተባበር ፈቃደኛ ባለመሆኗ ክሱን ለጊዜው እንዲቆም አድርጎታል፡፡ ውሳኔውን የሚቃወሙት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች አሁን ደግሞ ከምርጫ ጋር በተያያዘ በርካታ ወንጀሎች በተፈጸመባት ኢትዮጵያ ኦባማ ጉብኝት ሊያደርጉ መወሰናቸውን ፕሬዚዳንቱ የሚያወሩትና የሚያደርጉት ፍጹም የማይገናኝ መሆኑን እንደምታዊ አስተያየታቸውን በመስጠት ተቃውመውታል፡፡ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሥልጣን የሚይዝ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት በሥልጣን ላይ እያለ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ በምርጫ ዝረራ (መቶ በመቶ) አሸንፌአለሁ ከሚል አገዛዝ ጋር እንዴት እጅ ይጨባበጣሉ፤ እንዴትስ ለስብሰባ አብረው ይቀመጣሉ ከሚለው አስተያየት አኳያ የኦባማ ጉብኝት ካሁኑ በርካታ ተቃውሞዎች ገጥመውታል፡፡

አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ከሮበርት ኬኔዲ የፍትሕና የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል ያነጋገራቸው ጄፍሪ ስሚዝ ሲናገሩ “በዚህ ሳምንት ብቻ ሦስት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በተገደሉባት ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ኦባማ ጉብኝት እንዲያደርጉ መወሰኑ በጣም የሚረብሽ ነው” ብለዋል፡፡ ሲቀጥሉም “እንዲያውም ይህ ጉብኝት አሜሪካ የአፍሪካ አምባገነኖች ረዳት ነች ተብሎ የተሰጣትን ምሳሌነት ያጠናክረዋል” በማለት ለኤኤፍፒ ተናገረዋል፡፡

አገራቸውን ለ18 ትሪሊዮን ዶላር ዕዳ የዳረጉ ናቸው ተብለው በበርካታ አሜሪካውያን ዘንድ በምሬት የሚነሱት ኦባማ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት የገቡትን ቃል ሳይፈጽሙ መቅረታቸው መራጮቻቸው ያዘኑበት ጉዳይ ነው፡፡ አሜሪካውያን አሁንም ሥራ አጥነት ጎድቷቸዋል፤ አሁንም ኑሯቸው ከዕለት ወደ ዕለት እየወረደ መጥቷል፤ አገሪቱ የተሸከመችው ዕዳ ሊያስከትል የሚችለው ማኅበራዊና ሌሎች ቀውሶች ከግምት በላይ ሆኗል፡፡ በዚህ ዓይነት በምርጫ ዘመቻ ወቅት የገቡትን ቃል ያልፈጸሙ መሪ የአፍሪካ መሪዎችን በንግድ ጉዳይ ላይ ምን ብለው ነው የሚያማክሩት በማለት የኦባማን የኢኮኖሚ ፖሊሲ የሚቃወሙ ይጠይቃሉ፡፡ ወይስ አሜሪካንን እንዴት በዕዳ እንደነከሯት በማስተማር አፍሪካውያንም እንዴት የአሜሪካንን ፈለግ እንደሚከተሉ ነው የሚመክሯቸው በማለት ከፌዝ ጋር የተቀላቀለ አስተያየታቸውን የሚሰጡ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ (በአሁኑ ወቅት በአንዳንዶች ግምት የኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ ከ15 ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው)

ቡሽ በቦትስዋና ከቤተሰባቸው ጋር ባደረጉት ጉብኝት የዝሆን ኩምቢ ሲነኩ (Photo: TIM SLOAN/AFP/Getty Images)
ቡሽ በቦትስዋና ከቤተሰባቸው ጋር ባደረጉት ጉብኝት የዝሆን ኩምቢ ሲነኩ (Photo: TIM SLOAN/AFP/Getty Images)

በርካታ “የመጀመሪያው …” ማዕረግ የተጎናጸፉት ኦባማ (የመጀመሪያው ጥቁር ፕሬዚዳንት፣ የመጀመሪያው በሥልጣን ላይ እያለ የኖቤል ሰላም ተሸላሚ፣…) ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉዞ “በሥልጣን ላይ እያለ ኢትዮጵያንና የአፍሪካ ኅብረት የጎበኘ የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት” የሚል ሌላ “የመጀመሪያ” ማዕረግ ሰጥቷቸዋል፡፡

በሁለተኛው ዙር የሥልጣን ዘመናቸው ወቅት የአፍሪካን የዱር አራዊት በመጎብኘትና በመዝናናት በርካታ ፎቶዎችን ለቤተመጻህፍታቸው እንደተነሱት ጆርጅ ቡሽ፤ ኦባማም በኢትዮጵያ በሚያደርጉት “የመዝናኛ ጉብኝት”፤ “የአገር ባህል” ልብሳቸውን ከለበሱ የአፍሪካ “አምባገነኖች” ጋር የሚነሱት ፎቶ ወደፊት ለሚያቋቁሙት ቤተመጻህፍት ጥሩ የግድግዳ ማድመቂያ ይሆናል በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ አንድ የዓለምአቀፍ ግንኙነት ባለሙያ ተናግረዋል፡፡ (የፕሬዚዳንት ኦባማ Photo: Jacquelyn Martin/AP)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. mulugeta says

    June 20, 2015 02:42 pm at 2:42 pm

    Useless report, you should not post this at all dedeb

    Reply
  2. በለው ! says

    June 22, 2015 02:30 pm at 2:30 pm

    “በመፈቃቀርና በመፈቃቀድ ላይ በተመሠረተው የሰብዓዊ መብት መረጋጋጥ እኔም ያቺን ሀገር ሄጄ እረግጣለሁ ሲሉ ኦቦ ሁሴን አስታወቁ!”
    ምን ፍቅር አደረባቸው!?…
    ቅናት! እኮ ምን? ህወአት/ኢህአዴግ በሼክ አላሙዲን በኩል የተሸከሸከ ቼክ ለቢል ክሊንተን ፋውንዴሽን ማስገባታቸውን ሲሰሙ እኔስ በጡረታ ዘመኔ ለፋውንዴሽኑ የኢህአዴግን ራዕይ ማስቀጠል አዋጪ የወዲሁ የቅድመ ሥልጣን ላይ የቦንድ ግዢ (ኢንቨስትመንት) ያህል ነው ሲሉ አብራርተዋል።
    ለመሆኑ ከየትኞቹ የአፍሪካ መሪዎች ጋር ሊሰበሰቡ ይሆን?
    ከአልበሽር?ከኢሳያስ አፈወርቂ? ሮበርት ሙጋቤ? ባላፈው ነጩ ቤት ከመግባት ከተከለከሉት ጥቁር የአፍሪካ መሪዎች ኢትዮጵያ እንዳይመጡ ይከለከላሉን? ለትላልቆች የአፍሪካ ወንጀለኞች በዓለም ፍርድ ቤት አለመዳኘት ከለላ ያገኙት በትውልድ አፍሪካዊው ትንሹ ኦቦ ሁሴም ባራክ ጥበቃ ይሆን?ሞኝ የቀድሞ ያሜሪካ መሪዎች የዕርዳታ ስንዴ ሲልኩ ጡረታ ሳይወጡ ድርሽ አይሉም ለምን? ቻይና መንገድና የአፍሪካ ህብረት ህንፃን በነፃ ሠርታ እስክታስረክብና የአፍሪካን ግማሽ ገበያ በማልማትም በማዋለድም አስክትቆጣጠር በጉጉት ሲጠብቁ ይሆን አሁን ሕዝብና መሬቱን ሳይሆን ቀጠናውን በገዛ ገንዘብና የጦር መሳሪያዋ መግዛቷን ሲያቁ ባነው ተባነው ነው!?በፓርላ ውስጥ” አንደኛ ቻይና! ሁለተኛ ቻይና !ሶስተኛ ቻይና ያለው የኢኮኖሚስት ተጠቅላይ መሪ ማን ነበር?
    …..ኦቦ ሁሴን ባራክ በኬንያ የሚካሄደውን ዓለም አቀፍ የሥራ ፈጠራ ጉባዔ ከተከታተሉ በኋላወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ታውቋል፡፡*ኢትዮጵያ ነገር ፈጠራ!” ለሦስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ጉባዔ” ባለፉት ሁለት ጉባኤዎች ምን ተሠራ? ኢትዮጵያና ኢህአዴግ እንደሁ ከወለድ ነፃ!..በረጅም ግዜ የሚከፈል ብድር! ..በአነስተኛ ወለድ ብድር! ግማሽ ብድር ግማሽ ስጦታ!ከአፍሪካ አንደኛዋ ተመፅዋች ሀገር ይሉና…ከአፍሪካ አንደኛ…ከዓለም ሁለተኛ ያደገች የተመነደገች…ወጣቱ ዕድገቱን እየናቀ የሚሰደድባት…ደላላ እንደልብ ሰው የሚሸጥበት ልማታዊ ሙስና መር ኢኮኖሚ የተፈጠረበት ህዝቡ እንደ ጠ/ሚሩ ልዩ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ አገላላፅ ” ለኤርትራ አሰብ ወደብና የባድሜን መሬት..ለጅቡቲ ውሃና መብራት..ለኬንያ መብራትና ጥራጥሬ እህል ..ለሱዳን ለም መሬትና የቀንድ ከብት…ለግብፅ የአባይ ግድብ ቦንድ ተሰጠ ብሎ የሚጮህ…ምቀኛ ህዝብ ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር ናት ኢህአዴግ ዓላው ነው ምቀኞች!! ሲሉ ነገረውናል ኦቦ ሁሴን ባራክ በአንድ ወቅት ንግራቸው የኢትዮጵያ ገበሬ ትርፋማ ሆኗል! ልጆቹን ከፍሎ ያስተምራል! ድህነትን ተረት አድርጎ ለዓላም ምሳሌ ሆኗል ብለው ነበር አሁን እዚያ ገበሬ ቤት ሲበሉ ሲጠጡ እሳት ዳር ቁጥ ብለው ኩበት ጭስ እየጠገቡ አረቄ እየመጠጡ ሲያወጉ ማየት አለብን… ሂልተንና ሸራተን ባጅብ ተጎልቶ የብሔር ብሄረሰብ ዳሌ ሲናጥ መመልከትና መገልፈጥ ልማታዊ አፍሪካዊ የአሜሪካ መሪ አያሰኝም እንዲያውም ጥቁር የጥቁርን ሕዝብን መናቅና በጭቆናው መደሰት ትርፉ ትዝብትና ነው በለው!።ጥቁር አራት ነጥብ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule