• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይድረስ ለተገፋው ወገኔ !. . .

July 14, 2013 07:56 am by Editor 1 Comment

ይድረስ ትናንተም ሆነ ዛሬ ግፍ በነገሰባት ምድር ኑሮን በመከራ ለምትገፋው ወገኔ ! ይድረስ መልካም አስተዳደር ጠፍቶ በደል ለተጫነብህ ፣ ፍትህ ርትዕ ተዛብቶ የአስተዳደር ሚዛኑ ኑሮህን ላጨለመው ወገኔ ! ይድረስ ከዲስኩር  ባላለፈ  “የእድገት ስልጣኔ መንገድ እየተጓዝክ ነው ” ለሚሉህ ፣ ይድረስ ግልጽነት በጎደለው “መልካም አስተዳደር” ለምትረገጠው ታጋሽ ወገን፣ ይድረስ ትናንትም ሆነ ዛሬ ከአብራክህ ወጥተው አንተን ያልሆኑ ፣ ህመምህ የማያማቸው፣ በደልህ በማይገባቸው የመንግስት ምስለኔ ልጆችህ እየተሰቃየህ ላለህው ! ይድረስ የግፍ በደል ቀንበር ከትከሻህ ላልወረደልህ፣ ስቃይ መከራው ላላባራልህ ይድረስ ለከልታማው ወገኔ! ይድረስ የአንድ ጎልማሳ እድሜን በጭቆና መግፋቱ እያመመህም ቢሆን ለቻለከው፣ በቁጣ አመጻን ከመግለጽ ተገትተህ ጎስቋላ ኑሮን በዝምታ፣ በይሁንታ እየገፋህ ላለህው ወገኔ! በኮራህ በደላህበት፣ አክብረህ በተከበርክበት ቅየ ያ ክፉ ቀን አለፈ ስትል፣ ዛሬም ክፉው ቀን ተከትሎ  አበሳህን እያሳየህ ለምትገኘው ተገፊ ወገኔ!

ኑሮ ሳይደላህ አመጻን አለመምረጥህ እና በደልን በዝምታ ቁዘማ ማሳለፍን የመምረጥ ምክንያትህን ከቀየው የወጣሁ ነኝና አውቀዋለሁ ! ጎንደሬውም ሆንክ ወሎየው እንደቀረው ኢትዮጵያዊ በጨካኙ ወታደራዊ ጁንታ አገዛዝ ከአብራክህበወጡ ጨካኝ ልጆችህ የጋለ ብረት አለሎ ተቀጥቅጠሃል። ልጆችህ ታስረው ርህራሄ በሌላቸው የአገዛዙ አቀንቃኞች ቁም ስቅላቸውን እያዩ ተገርፈዋል። በግፍ የተገደሉ ልጆችህን አስከሬን በወጉ እንዳትቀብር ተደርገሃል። መሽቶ እስኪነጋ በጨካኞች አረመኔያዊ የቀይ ነጭ ሽብር ዘመቻ ባሩድ የተረሸኑ ልጆችህ ደም ጉራንጉሩን፣አውራ ጎዳናዎችና አደባባዩን አጨቅይቶት የከፋ የሽብር ጊዜ አሳልፈሃል፣ አይገፋ የለም ቁጣህን አምቀህ ክፉውን ቀን በሆደ ሰፊነት  ገፍተሃል! በዚያ ክፉ ዘመን የስጋ ክፋይ ወንድሞቸን ፣ “የት ይደርሳሉ!” የተባሉ የዘመድ አዝማድ ጎረቤት ትንታግ ወጣቶችን በግፈኛው አገዛዝ የተነጠቁ ወገኖች አካል ነኝ ። ስለዚያ ዘመን የወላድ መከራ የማውቀው ጥቂት ባይባልም፣ ሰለነበረው ስርአት አስከፊነት የታሪክ መዛግብት አገላብጫለሁ ፣ የአይን እማኞችን “አህ” ብየ አድምጫለሁ! ከሁሉም በላይ የልጆቻቸውን የሞት መርዶ ለመስማት ብርቅ ሆኖ ሳይሳካላቸው ከቀሩት እናቶች መካከል ልጅ ብሆንም ያኔ የእኔዋን እናት እንባ አልረሳውም! በድህነት ቤት ልጅ ወልደው ፣አሳድገው በሞት ሲነጠቁ ለመቅበር ሳይታደሉ የቀሩት እናቶችን ቤት ይቁጠረው። ማቅ ለብሰው ማቅ መስለው አመታትን የገፉ እናቶች አብራክ ውጤት ነኝና የዘመኑን ስርአት ክፋት ጭነት አውቀዋለሁ። በዚያ የግፍ ዘመን በቀሩት የሃገሪቱ ክፍል እንደሆነው ሁሉ በጎንደር በጎጃም እና በወሎ ዋና ከተሞች ያለተወሰነው የግፍ እርምጃ በገጠር የወረዳና የአውራጃ ከተሞች በወጣቱ ደም የጨቀዩበተት ዘመን ፍጹም አይረሳም ።

ወገኔ ሆይ ! እዚህ ባደረሰህ መንገድ ለጋ ወጣት ልጆችህን ገብረሃልና የዛሬው ዝምታህ አይደንቀኝም ። በግፍ ጭቆናው ዘመን የሌሊቱ ጥይት እሩምታ በረድ ሲል የማለዳው ደሮ ሲጮህ ሬሳ የመፈለጉ አሰቃቂ የታሪክ ሂደት እንደ ቀረው የኢትዮጵያ ወገንህ ምሬት ሃዘንክን ጠባሳ ጥሎብሃልና ዛሬ አንገት መድፋት መቆዘምህ አያስደንቀኝም። ዛሬም ዘመን ከፍቶህ ዳግም ትንታግ ልጆችህን አንዳታጣ ስጋት ሆኖብህ ዝም በማለትህ “ሃሞትህ ፈሰሰ!” እያልኩ ላሳብቅብህ የረከሰ  ሰብዕናን አውርሰህ አላሳደግከኝምና ፣ በቁዘማ ዝምታህ አልፈርድም ። በከተማ ባሩድ እና ባልጠቀመን የእርስ በርስ ጦርነት የአብራክህን ክፋይ ልጆችህን በጆፊ አሞራ የተነጠቅክ የህብረተሰብ ክፍል ነህና ህመምህ ህምሜ በመሆኑ ይገባኛል። እናም የዛሬ ህመም ስጋትክን አሳምሬ አውቀዋለሁ ! እናም ” ለምን ግፍ ሲጫኑህ  በዝምታ ትቆዝማለህ? “ለማለት አይዳዳኝም! ያኔ! ያ ክፉ የደርግ ስርአት ያከትም ዘንድ ሃዘንክን ሃዘን አድርገህ በአገዛዙ ላይ አኮረፍክ ፣ ዳሩ ግን ልክ እንደ ዛሬው በዝምታ ቁዘማ አንገትክን ደፍተህ ግን አልተቀመጥክም ። ለምስክር የተረፉ ልጆችህ ለመስዋዕት በማዘጋጀት መርቀህ ወደ መራራው ትግል መርቀህ ላክካቸው ፣ እኒያ አንበሶች ተራራ ቋጥኝ ቧጠው ፣ ሸንተረር ወንዙን ተጋፍተው ተሻግረው ብሩህ በመከባበር የተገነባች ኢትዮጵያን ይፈጥሩ ዘንድ ነበር ።

መራራው መስዋዕትነት በደም ተከፍሎ ያገኘህውን ውጤት ቢያሳዝንም ለሰላም ሲባል ይሁንታህን ሰጠህ ! ዲሞክራሲ ተሰብኮ እንለይ ያሉት ተለይተው፣ሃገሬው በቋንቋ ሲደለደል ሌላ መከራ ለመምጣቱ ምልክቶች ቢታዩም ይህንንም ይሁን አልክ! ለሰላም ለእድገት ሲባል! የሰቆጣ አላማጣው ፣ የሁመራና የወልቃይት ጠገዴውን ክፍፍልም ሳትመርጥ ፣ ሳትወድ የተጫነብህ ቢሆንም ይህንንም በዝምታ ቁጭት አለፍከው ! ያልቻልከውን ህመም የመጣብህ ፣ ከአመታት በፊት ከሱዳን የሚዋሰነው ድንግሉ የሃገርህ መሬት ከፍትህ ርትህ ውጭ ሃገሬው እየተፈናቀለ ለሱዳን እንዲሰጥ መደረጉ ነበር። ይህ አስቆጭቶ ቢያንገበግብህም ዝምታ ቁዘማህ ዛሬም ትዕግስት መሆኑን የሚረዱ ምስለኔዎችን አልታደልክም!

እናም የደም ክፋይ ነኝና ምክሬን ትሰማ እማጸንሃለሁ ! የተሰጠህን ዲሞክራሲያዊ መብት ተጠቀምበት ! ዝምታ ቁዘማውን ፣ ቁጭት ንዴት አቤቱታህን በሰላማዊ ተቃውሞዎች ሁሉ ተሰልፈህ ጥያቄዎችህን ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጽህን ከፍ አድርገህ በማሰማት ዝምታህን ትሰብር ዘንድ እመክርሃለሁ!

ኑሮህ ከድጡ ወደ ማጡ የመሆኑን ግራ አጋቢ እንቆቅልሽ የአደባባይ ሚስጥር ሆኖ እያለ ፣ ድህነት እና ስራ አጥነት በሃገር ነግሰው ፣ ኢኮኖሚ የሚሉት “አደገ !” ይሉናል ። ለእድገቱ ዋቢ ደግሞ በኑሮውን ጣራ መንካት የተደቆስውን ያንተን  ጓዳ የማያውቁት የአለም ገንዘብ ድርጅት እና ከአመት አመት የሚሰጠው የእድገት ቁጥር ከፍ ማለት ብቻ ነው ። ምድር ላይ ያለውን እውነታ ግን ከሚባለው የተለየ ነው! የኢኮኖሚው ብቻውን ማደግ ከመንገድና ከፎቅ ግንባታ ያለፈ ላለመሆኑ ብዙ ማለት ይቻላል ። የኢኮኖሚው ማደግ በአንተ በዜጋው የለት ተለት ኑሮ ላይ የማይታይ የማይዳሰስ ለመሆኑ ለማንም የተደበቀ አይደለም ። በኑሮው ጣራ መንካት ፣ በድህነቱ፣ በመልካም አስተዳደር እጦትና በስራ አጥነት ምክንያት እኔ ወዳለሁበት አረብ ሃገር ብቻ ያለ ህጋዊ ማዕቀፍ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ እድሜያቸው ለአቅመ አዳም ያለደረሱት ዜጎች በህጋዊ ኮንትራት ስም ተሰደዋል። እኒህ አብዛኛው ከገጠሩ የሃገራችን ክፍሎች በደላላ ተግዘው የመጡት አብዛኛው ሴት እህቶች እድሜያቸውን ቆልለው ሲሰደዱ እንኳ ከልካይ የለም። ይህ ብቻ አይደለም ። ለስራ ወደ ስለሚሔዱበት ሃገርም ሆነ ሰለሚሰሩት ስራ በቂ መረጃ አይሰጣቸውም! ችግር ቢገጥማቸው ለማን አቤት አንደሚሉና ወዴት እንደ ሚሄዱ አያውቁም! የመልካም አስተዳደሩ እና የመንግስት ተቀቋማት ግልጽነት ብሎም ተጠያቂነት አለመኖር ድህነት እንዳሸሸው ዜጋ ድንበር ለመሻገሩ ብዙ አመላካች መረጃዎችን ማቅረብ እችላለሁ ! በዋናነት የሚነሳው ዜጎች ከሃገር በስራ ኮንትራት ከመላካቸው አስቀድሞ በሃገሮች መካከል ግልጽ ስምምነት አለመደረጉ ነው። በዚህ ሁኔታ የተሰደዱትም ቢሆን የመብት ጥሰት ሲገጥማቸው አቤት ብለው ወደ ፍትህ የሚያቀርባቸው የተዳራጁ ሚስዮኖች አሉ ከማለት የሉም ማለት ይቀላል !

ወገኔ ሆይ! የዜጎች የከፋ ስደትና የመብት ጥበቃ ጉድለት መፍትሔ ያገኝ ዘንድ ለመንግስት ያለመታከት ተናግሬ ፣ መክሬ ፣ ዘክሬ የሰማኝ የለም! እናም ይህ በአብራክህ ክፋዮች ላይ እየደረሰ ላለው በደል በማናቸውም ስብሰባም ሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ተሳትፎ በማድረግ ድምጽህን እንድታሰማ እመክርሃለሁ! አማጸንሃለሁ!  የህዝብን ድምጽ የሚሰማ መንግስት ይስጠን!

ከሰላምታ ጋር

ነቢዩ ሲራክ
ሃምሌ 2005 ዓም ሳውዲ አረቢያ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    July 17, 2013 08:43 pm at 8:43 pm

    Say no to woyane ethnic fascists if you really care for Ethiopia and Ethiopians. Ethiopian Problem is immense and could not be solved by excluding millions and forcing them to live the Country. It is my dream and could have contributed a bit to the solution of Ethiopian Problem if the Country was not ruled/misruled by the home grown fascists.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule