• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦህዴድ ሳያገግም፤ ብአዴን ሊደገም?

March 7, 2016 07:03 am by Editor 3 Comments

ኢትዮጵያን በተገንጣይ ስም የሚመራው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት፣ የገጠመው ቀውስ እየተለጠጠበት ነው። ኦህዴድ አደረጃጀቱ ሊጠገን በማይችልበት ሁኔታ ተናግቶበታል። ይኽው ወረርሽኝ ወደ ሌሎች ገባር ድርጅቶች መስፋፋቱ የማይቀር ቢሆንም ብአዴን ውስጥ ቀውስ ስለመነሳቱ መረጃዎች ከቀድሞው በላይ ጎልተው እየወጡ ነው።

በ1997 ምርጫ ኢህአዴግን ከውድቀት ጉድጓድ ያወጣው ኦህዴድ፣ ህወሃት በአንጃ ተቧድኖ ሲባላ የመለስን ወገኖች የታደገው ብአዴን አሁን ለህወሃት መከራ ሆነውበታል። አጋር የሚባሉት ድርጅቶችም ውስጥ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ የራሱ የህወሃት መገናኛዎች እየመሰከሩ ነው።

የችግሩ አሳሳቢነት ቀላል ባለመሆኑ ኦሮሚያና ጋምቤላ ተሸንሽነው “በጊዚያዊ ወታደራዊ አስተዳደር” ሥር ወድቀዋል። ይህንኑ እውነት አሁንም የራሱ የህወሃት ልሳኖች አምነው ይፋ አድርገውታል። አንድ ወጥ አገር በነጻ አውጪ ቡድን፣ በፌዴራል መዋቅር፣ በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር፣ በሱዳን ሚሊሺያ፣ ወዘተ የተዘበራረቀ አመራር ላይ መውደቋ የወደፊቱን የመለስ “ራዕይ” አመላካች ስለመሆኑ አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ነገሮች እንደዚህ በጦዙበት ወቅት “የታላቋ ትግራይ” ድንበር ሙሉ የሁመራን ለም ምድር የሚያጠቃልል፣ ጠገዴንና ወልቃይትን የሚውጥ፣ እንዲሁም ኤርትራ ግዛት ጠልቆ የሚገባ መሆኑ ቦታና ስም ተዘርዝሮ ይፋ መሆን ጀምሯል። በሌላ ጎኑ ኦህዴድ ውስጥ “ህዝብ ለምን አመጸ፣ የጸጥታ ሃይሉ እንዴት ከጃችን ወጣ? የታች መዋቅሩ እንዴት ፈረሰ? ድርጅታዊ ሠንሰለቱ እንዴት ተበጠሰ? ታማኝነትና ጠባብነት …” ማለቂያ የሌለው ግምገማ  እየተካሄደ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ  የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚና የኦህዴድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ፣ የኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚና የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ኩቹ ለጊዜው ከተመደቡበት ያገለጋይነት ሹመት ተነስትው ቀለበት ውስጥ እንዳሉ ተሰምቷል። ሹም ሸሩ ቀጣይ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

በህወሃት አደረጃጀት “ጸጥታ” የሚለው ሹመት የስለላው ምሶሶ ዘርፍ ነው። የኦህዴድ የፀጥታ ሃላፊ ተነሱ ማለት ስለላው ተናግቷል ወይም እንደ ቀድሞ መረጃ አያገኝም ማለት ነው። ይህ የሚሆነው ደግሞ አንድ ለአምስት የሚባለው የስለላ መዋቅር ውሃ በለቶታል ማለት ነው። አሁን እንደ አዲስ ቢደራጅ የሚተገበረው ቀድሞ ታች ባሉት አመራሮችና ካድሬዎች ላይ በመሆኑ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም በማለት ስለ አደረጃጀቱና ስለ ወቅቱ ግለት የሚያውቁ እየገለጹ ነው።

በየቀበሌው ድምጻቸውን ያሰሙ ወገኖች ተገልለዋል፤ በሺህ የሚቆጠሩ ታስረዋል። የተሰደዱ፣ ቀያቸውን ጥለው የኮበለሉ፣ ዱር ያሉ፣ ከዚህም በላይ ሃዘን ያደቀቃቸውና የሚጠዘጥዛቸው ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ የወንዝ ልጆች፣ ኦሮሞዎች፣ ኢትዮጵያውያን አዝነዋል። የቂም ቋጠሯቸው ጠብቋል። የፈሰሰው ደም ከሚያንዘፈዝፋቸው  ክፍሎች መካከል የታችኛው ካድሬና አመራር በግንባር ቀደምትነት የሚሰለፍ ነው። በዚህ መነሻ ህወሃት እነዚሁ ዜጎች ላይ ታዛዥ ሃላፊ ቀይሮ እንደ ቀድሞው ልፈንጭ፣ ለጋልብ፣ ልፍለጥ፣ ልቁረጥ ቢል አይሳካለትም ሲሉ እነዚሁ ክፍሎች ያብራራሉ።

ምሳሌ ሲያነሱ አርሲ የሆነውን ይጠቀሳሉ። የኦሮምያ ፈጥኖ ደራሽ አባል ወገኖቹን ሊገድል የመጣውን የአጋዚ ቅጥረኞችን መሳሪያ አዙሮ ረሸነ። አስራ አንዱን ሲገድል አንዱን አንገቱ ላይ ቆሞ ነው እያቀራራ ጥይት ያዘነበበት። ተቺዎች እንደሚሉት የዚህ ፖሊስ ተግባር መጪውን የሚያመላክት ነው። ህወሃት ብቻ ሳይሆን ሌሎችም በብሄራቸው ላይ የሚፈጸም ግፍ ያማቸዋል። በዝርፊያ የበሰበሱትን ሳይጨምር።

የበታቹ ካድሬ የዝርፊያ ጉዳይ አያሳስበውም። አብዛኛው ደግሞ ይህ የህብረተሰብ ከፍል ነው። ባንድ ግምገማ ላይ አንድ የህወሃት ሰው ስለ ሙስና አንስተው ሲገመግሙ አንድ ከንቲባ ተነስተው “እርስዎ ቤተሰቦችዎን እየላኩ መሬት ይወስዱ አልነበረም” ሲል ሞግተዋቸው እንደነበር የሚያስታውሱ “አሁን የበላዩ የበታቹን ሲገመግም አዳራሹ በሽሙጥ ይሞላል፤ ሌላውን ለመወንጀል ንጹህ ጀርባ ያላቸው ስለሌሉ የሚታየው ሁሉ ከበሰበሰ እንቁላል ጫጩት የመከጀል ያህል ነው” በሚል ህወሃት ብስባሽ ላይ ሆኖ እንደሚወራጭ ያስረዳሉ።

በኦሮሚያ መዋቅር ፈርሶ ሽማግሌዎች መሬት ለተወሰደባቸው ሲያከፋፈሉ ነበር። አጋርፋ አካባቢ ይህ ተፈጽሟል። ይህንን ህዝብ መልሶ ማደራጀት ጅልነት እንደሆነ የሚጠቁሙ ክፍሎች ህወሃት በቅጡ አስቦና መክሮ ወደ ትክክለኛው መፍትሄ ሊመጣ እንደሚገባው ይመክራሉ። አያይዘውም በሌሎች የህብረተሰብ ከፍሎች ላይ የሚፈጸመው ግፍ አድሮም ቢሆን ዋጋ ስለሚያስከፍል በስማቸው የሚፈጸመው ወንጀል ይቆም ዘንድ የትግራይ ንጹሃን ድምጻቸውን ሊያሰሙ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

አማራ ክልልም ቢሆን የተሳከረ ችግር ስለ መኖሩ ህወሃት የማይክድበት ደረጃ ላይ ነው። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ፐሬዚዳንት የአማራ ክልል አስተዳዳሪን ውይይት ላይ “አማራን ትጥቅ አስፈታ” የሚል ትዕዛዝ አዘል ንግግር ሲናግሩ “የምን ትጥቅ ነው የማስፈታው? አንተ ግምጃ ቤት ከፍትህ ለትግራይ ህዝብ መሳሪያ እያደልክ” የሚል መልስ እንደሰጡ በተለይ ለጎልጉል መረጃ የላኩ አስረድተዋል።

የወልቃይትን ጉዳይ ከህወሃት ፍላጎት አንጻር የብአዴን ስራ አስፈጻሚ እንዲቀበልን አቋም እንዲይዝ ትዕዛዝ ቢሰጥም “በቀጥታ ከህዝብ ጋር የምንገናኘው እኛ ነን፤ ይህንን አንቀበልም፤ ልታስፈጁን ነው?” የሚል ምላሽ ከበታች ካድሬዎች ተሰንዝሯል። እንደ ዜናው አቀባዮች ከሆነ ብአዴን ውስጥ ኦህዴድ ላይ የደረሰው የበታች አመራር መንሸራተት እየታየ ነው።

የብአዴን ማዕከላዊ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጓል፡፡ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ፣ ከቅማንት ማኅበረሰብ ማንነት ጋር በተያያዘ የተከሰተውን ችግርና የግጭት አፈታት ተግባራትን፣ በአማራና በትግራይ ክልሎች በፀገዴ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግርና በሁለቱ ክልሎች የተደረገውን ምክክር፣ በክልሉ በድርቅ የተጠቁ 2.3 ሚሊዮን ዜጎችን በተመለከተና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ለሦስት ቀናት መክሯል ሲል ሪፖርተር ዛሬ ዘግቧዋል።

ሰሞኑን በሁለት የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ላይ በተወሰደው እርምጃ የተጀመረው ኦህዴድን የማጽዳት ተግባር በርካታ የአመራሮች ላይ ሰይፉን እንደሚያሳርፍ ከወዲሁ የሚያመላክቱ በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡ ከሁለት ወር ተኩል በፊት ጎልጉል የኦህዴድ ህወሃት/ኢህአዴግን መክዳት አስመልክቶ በጻፈው የዜና ዘገባ ላይ እስካሁን የተሠራው ጥርነፋም ሆነ የህወሃት የበላይነት የተፈለገውን ውጤት ሳያመጣ ቀርቶ ኦሮሚያን ለከፋ ችግር እንደዳረጋት ተጠቅሶ ነበር፡፡

ይህ የኦህዴድ ችግር ገና መስመር ሳይዝ አሁን ደግሞ ህወሃት ወደ ብአዴን ላይ ለመዞር ማሰቡና “ትጥቅ” ለማስፈታት የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጉዞውን ከድጡ ወደ ማጡ ያደርገዋል የሚለው አስተያየት የበረከተ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ ኦህዴድና ብአዴን አብረው ህወሃትን ብቻውን ቢያስቀሩት የፖለቲካውን አሰላለፍም ሆነ የአገሪቱን የወደፊት አቅጣጫ ባልታሰበ መልኩ ይቀይረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ (ፎቶ: addisfortune)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Aman says

    March 7, 2016 12:03 pm at 12:03 pm

    የናንተው የብዕር ጥቃት በ25 ዓመታት ውስጥ ምንም ሊሰራ ኣልቻለም። እናንተ እንደምትፎኩሩት ከሆነ ወያነ ከኣስርቱ ዓመታት በፊት ሞቶዋል።

    Reply
  2. gud says

    March 7, 2016 04:01 pm at 4:01 pm

    Speculation and wishful thinking

    Reply
  3. geresu says

    March 10, 2016 10:35 am at 10:35 am

    ወያኔ ብአዲኖችንና ኦህዲድዶችን ንፍጣቸዉን እያናፈጣቸዉ ነዉ::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule