• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለአገር ሰላም መፍትሔው …

September 24, 2016 01:18 am by Editor 1 Comment

እኔም እንደ ዜጋ ለአገር ሰላም  አለኝ!!

ኢትዮጵያ የምትባል አገር የሁላችንም እንጂ የተወሰኑ ግለሰቦች፣ ብሔሮች፣ ጎሳ፣ ዘር፣ …. አይደለችም፡፡ የተወለድኩት በንጉሡ ዘመን ሲሆን፣ ነፍስ ያወኩትና ፊደል የቆጠርኩት በደርግ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ ደርግ እጅግ ክፉና ጨካኝ ወታደራዊ መንግሥት እንደ ነበር አስታውሳለሁ፡፡ ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ብዙዎች ተገድለዋል፤ ተረሽነዋል፡፡

በአንጻሩ አሁን ያለው መንግሥት ከደርግ በምን ይሻልል? ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል፡፡

ደርግ በአርሶ አደሩና በከተሜው ሕዝብ ዘንድ አንጻራዊ በሆነ መልኩም ቢሆን ተቀባይነት ነበረው፡፡ በተለይ አገራዊ አጀንዳን በሚመለከት ሕዝቡ ከመንግሥት ጎን ቆሞአል፡፡ በ1969 ዓ.ም ትዕቢተኛው የሶማሊያ ወራሪ መንግሥት ኢትዮጵያን በወረረችበት ጊዜ ሕዝቡ አዎንታዊ ምላሽ ሰጥቶአል፡፡ ወረራውን ለመቀልበስ የሕዝቡ ድጋፍ ከደርግ መንግሥት ጋር ስለነበር በአጭር ጊዜ ውስጥ ወራሪውን ጦር ከአገር ጠራርጎ ያስወጣ ጀግና  ሠራዊት ሆ! ብሎ ተነሥቶ ገድሉን ለዓለም ሕዝቦች አሳይቶአል፡፡

ይሁን እንጂ በደርግ ዘመን የነበሩ የሠራዊቱ አባላት በጦርነት የመሰልቸት ጉዳይ እንደነበር አይካድም፡፡ በደርግ ውስጥ በነበረው ሽኩቻና መሰልቸት ምክንያት ወያኔ አጋጣሚውን ተጠቅሞ መላውን ኢትዮጵያ መቆጣጠር ቻለች፡፡ ወያኔ ለአገዛዝ እንዲመቻት በፌደራሊዝም ሰበብ ኢትዮጵያን በክልል ከፋፈለች፡፡ ዓላማው የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ መመለስ የሚል መርሐ ግብር ነበር፡፡ ሆኖም የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ ተመልሶአል ማለት አያስደፍርም፡፡ የብሔሮች ጥያቄ ቢመለስ ኖሮ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በጋምቤላ እና በሌሎችም ክልሎች አሁን እየታየ ያለው ሁኔባልተከሰተ ነበር፡፡

ስለዚህ በግልፅ እንደሚታየው በወያኔ መንግሥት እና በሕዝቡ መካከል መጠነ ሰፊ ክፍተት ታቶአል፡፡ ኢትዮጵያም በአደጋ ላይ ትገኛለች፡፡ ሕዝቡ ጥያቄ አንግቦ ሆ! ብሎ ተነሥቶአል፡፡ የሕዝቡን ጥያቄ የወያኔ መንግሥት መመለስ አልቻለም፤ ወይም ደግሞ ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡

ስለዚህ እኔም እንደ ዜጋ ለአገሪቱ ሰላም የመፍትሔ ሐሳብ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡

1. ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በሁሉም የአገሪቷ ክፍሎች የታሰሩት እንዲፈቱ፤

2. የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት የሚለው የወያኔ ፓርቲ ስም በአስቸኳይ መቀየር አለበት፤ ምክንያቱም ነፃ የመውጣት ዓላማ ከማን ነው? መቼ ነው? ይህ የሚያሳየው ወያኔ የራሱ ብቻ የሆነ ድብቅ ዓላማና አጀንዳ እንዳለው
አመላካች ነው፡፡

3. ወያኔ እኔ ከለሌሁ አገር ትፈርሳለች፤ ኢትዮጵያ ልክ እንደ ሶማሊያ፣ ሊቢያ፣ ሶሪያ፣ … የሽብርተኞች መፈንጫ ትሆናለች የሚለው ፕሮፓጋንዳ መቆም አለበት፤

4. ወያኔ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ መደራደር አለበት፤

5. ወያኔ የትጥቅ ትግል ላይ ከሚገኙት ጋር በድርድር ሰላም የሚፈጠርበትን መፍትሔ መፈለግ አለበት፤

6. ወያኔ እኔ ብቻ አገር አመራለሁ፤ አስተዳድራለሁ … ማለት ትክክል አይደለም፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንጂ ባዕድ
በአገራችን የለም፤

7. ፌደራሊዝም ለኢትዮጵያ መልካም እንደሆነ ይታመናል፡፡ ሆኖም ብሔር ተኮር የፌደራሊዝም ሥርዓት ፈርሶ መልክዓ ምድራዊ ይዘት ያለው የፌደራሊዝም ሥርዓት እንዲካሄድ መፈቀድ አለበት፤

8. አሁን ያለው የምርጫ ቦርድ ፈርሶ ገለልተኛ የሆነ የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚሽን መቋቋም አለበት፤

9.  ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ሥልጣኑን መልቀቅ አለበት፤

10. ሁሉንም የሚያሳትፍ የሽግግር መንግሥት መቋቋም አለበት፤ ይህ ማለት በሰላማዊ እና በትጥቅ ትግል ለሚታገሉ ሁሉ በር መከፈት አለበት፡፡ አገራዊ አጀንዳ ያላቸው ሁሉ መሳተፍ አለባቸው፡፡ ለኢትዮጵያ ሰላም ሲባል ዝቅ ማለት ያስፈልጋል፡፡

11.  አሁን በሥልጣን ላይ ለሚገኙ የወያኔ ባለ ሥልጣናት በሰላማዊ መንገድ፣ ለአገር ሰላም ሲባል ሥልጣን በመልቀቅ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም ካመቻቹና ፈቃደኛ ከሆኑ ከዚህ በፊት ለፈጸሙት ወንጀል ተጠያቂ እንዳይሆኑ የደህንነት ዋስትና ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ እስከ መቼ እየተጣላን፣ እየተብላላን፣ አንዱ ሥልጣን ሲይዝ ሌላው ወህኒ የሚጣልበት ዘመን ማብቃት አለበት፡፡

በቃ! በኢትዮጵያ ጦርነት፣ ረሃብ፣ ጥላቻ፣ የዘር ልዩነት፣ ጎሰኝነት፣ …. ታሪክ መሆን አለበት፡፡

እውነቱን ለመናገር እነዚህን ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ከተቻለ ጥቅሙ ይበልጥ ለወያኔ ባለ ሥልጣናት ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች ከአርባ ዓመታት በላይ ያለ እረፍት በፖለቲካ ሕይወት ሲሳተፉ የቆዩ ስለሆኑ ዕረፍት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ባለትዳርና የልጆች አባት /እናት/ ናቸው፡፡ ሰላማዊ ኑሮ በመኖር ልጆቻቸውን አሳድገው ወግ ማዕረጋቸውን ማየት አለባቸው፡፡ ሥልጣንን የሙጥኝ ብሎ መያዝ አስፈላጊ አይደለም፡፡ የአምባገነን የአፍሪካ መንግሥታት የጭካኔ አሠራር በኢትዮጵያ መታየትና መደገም የለበትም፡፡ ሰላማዊ ሕይወት መኖር አለብን፡፡ የትጥቅ ትግል ያነሱ ሰዎች ጥያቄአቸው በሰላማዊ መንገድ ከተመለሰላቸው ከጫካ ምን ይሠራሉ? ይምጡ፤ ከተማ ይግቡ፡፡

ከወዳጅ ዘመድ ጋር ይቀላቀሉ፡፡

በመሠረቱ ወያኔዎች ለአስራ ሰባት ዓመታት የታገሉት ትግራይን ለመገንጠል ነበር፡፡ የትግራይ ነፃ መንግሥት የማቋቋም ሕልም ነበራቸው፡፡ ሆኖም ትግራይን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠሩ በኋላ ትግራይን ብቻ መገንጠል አላረካቸውም ነበር፡፡ ለካስ መላውን ኢትዮጵያ መቆጣጠር ይቻላል የሚል አዲስ ራእይ ተከሰተላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ተሳካላቸው፡፡

ነገር ግን ምን ለውጥ መጣ? እንጠይቅ!

ምንም ዓይነት ለውጥ አልመጣም፡፡ ወያኔ ደርግን አስወግዶ እራሱ ሌላኛው ደርግ ሆኖ መጣ! ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር በዘር ከፋፍሎና ሰነጣጥቆ በሕዝቦች መካከል ከፍተኛ የሆነ ጥላቻ እንዲነግሥ አደረገ፡፡

እንግዲህ የቀረበውን የመፍትሔ ነጥቦች ተግባራዊ ካልሆነ በመጨረሻ ሕዝብ ማሸነፉ አይቀሬ ይሆናል፡፡ ለሚደርሰው ጥፋትና ውድመትም ተጠያቂው የወያኔ  ባለሥልጣናት ይሆናሉ፡፡ የመጨረሻ ዕድላቸው ወህኒ ቤት እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ ከዚህ ውጪ ግን ሥልጣን በሞኖፖል ይዤ ዘላለም እኖራለሁ ብሎ ማሰብ እጅግ ሞኝነት ነው፡፡

ሕዝቦችን አፍኖ ለዘላለም መግዛት አይቻልም፡፡ የሕዝቦች ጥያቄ በበቂ ሁኔታ መመለስ አለበት፡፡ ወያኔዎች  ይህን የመፍትሔ ሐሳብ ቢሰሙና ቢቀበሉ፣ አገር ሰላም ትሆናለች፤ ትረጋጋለች፡፡ ከዚህ ውጭ የክልል መሪዎችን መቀየር ሥር ነቀል ለውጥ አያመጣም፤ እንዲህ ማድረግ የሕዝቦችን ጥያቄ አይመልስም፡፡ ጉልቻ ቢለወዋጥ ወጥ አያጣፍጥ እንደሚባለው ዓይነት ብቻ ይሆናል፡፡

ነገር ግን ያለ ምንም ለውጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ አሁን ባለው መልኩ እንዲቀጥል ከተፈለገ እጅግ አደገኛ ሁኔታ እንደሚከሰት ከወዲሁ እንደ ነቢይ መተንበይ ይቻላል፡፡

የመፍትሔ ሐሳቡ ተቀባይነት እንዲያገኝ ምኞቴ ነው፡፡

ደጉ ዘመን

ከአዲስ አበባ – ኢትዮጵያ

E-mail: deguzemen@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Takele says

    September 28, 2016 06:20 pm at 6:20 pm

    Degu Zemen

    Your opinion is appreciated . We need people like you who have positive attitude to find means and ways of aborting the worst situation created in our country . As you know this serious situation should not leave for a certain group of individuals , we all have to cooperate and unite to bring those antagonistic groups together and have valuable discussion . Let us wish our country to have a better future and good name . Our beautiful country is naturally gifted from the Almighty God . Let us make the people of Ethiopia lead a better life and see a better tomorrow . Let us make the new generation be wise , healthy and wealthy , avoid atrocity , narrowness( confined in a thin ethnic group ) selfishness , above all power monger . There are a couple of organization’s who are trying to bring peace and justice for Ethiopia , so cooperate with Peace and Justice for Africa (PJA)
    and share ideas .

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule