• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተካደ ትውልድ

January 23, 2017 08:13 am by Editor 2 Comments

የተካደ ትውልድ
አይዞህ ባይ የሌለው
ታዳጊ የሌለው
ወይ ጠባቂ መላክ፤ ወይ አበጀ በለው
ደርሶ ከቀንበሩ የማይገላግለው

የተካደ ትውልድ፤
አብዝቶ የጾመ፤ ተግቶ የጸለየ
ጥቂት  መና ሳይሆን፤ ጥይት ሲዘንብ ያየ
እድሜ ይፍታህ ተብሎ፤ የተወለደ’ለት
አምባሩ ካቴና፤ ማተቡ ሠንሠለት፡፡
ምቾትን የማያውቅ፤ ረፍት የተቀማ
አልጋው ያጋም እሾህ፤ ምኝታው የሣማ

የተካደ ትውልድ፤

ሞቶ እንኳ ሬሳው፤ አይላላለት ቀንበር
በዘብ  እጅ ተገድሎ፤ በሹም የሚቀበር
ከጡት አስጥል በላይ፤ ኑሮ የመረረው
እንዳይሄድ፤  ጎዳናው፤ የተደናገረው
ድል ያልሰመረለት ትግል ሳይቸግረው

የተካደ ትውልድ
በሥጋ በነፍሱ
በቀልቡ በገላው
ኧረ ምንድን  ይሆን ፤ ምንድን ይሆን መላው?

(በዕውቀቱ ሥዩም)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    January 24, 2017 04:37 pm at 4:37 pm

    በእዉቀቱ ሥዩም እጥር ምጥን ያለችውን የግጥም ስንኝህን አነበብኳት። የግጥምህ የመጨረሻ መደምደሚያ በጥያቄ የተቋጨ መሆኑን ሳይ ለጥያቄህ መልስ ይሆን ዘንድ ይሄንን ለመፃፍ ወደድኩ።

    መላው እንደ አያያዙና እንደ አመጣጡ ቆርጦ መታገል ብቻ ነው። የነጻነት ዋጋ ውድ ነው ። በ ዉድ ዋጋ የሚገኝ ነገር ደግሞ ዉድ ህይወትን ሁሉ ይጠይቃል። ዓለማችንን ከጥፋት ማዕበል ተመልሳ እንደትቆም ያደረገው ልዩ ተምሳሌችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውድ ህይወቱን ከፍሏል። ኢየሱስ ክርስቶስ ለስው ልጆች መዳን ሲል ዉድ ህይወቱን ሁሉ ከፍሎልናል ብለው የሚያምኑና የሚከተሉት ምዕመናን ዛሬ በዓለማችን ላይ ብዙሃን እና ለቁጥር የሚያታክቱ ናቸው። የስው ልጅም እንዳለከው በተፈጥሮው ሰው በመሆኑ ብቻ ሊያገኘው የሚገባውን መብቱን የተነጠቀ ሲመስለውና መነጠቁን ካወቀ ለነጻነቱ ሲል “በሥጋ በነፍሱ በቀልቡ በገላው” መስዋትንነትን ክፍሎ የነፃነቱ የመብቱ ባለቤት መሆኑ አይቀሬ ነው። ይሄንን አይቀሬነት እስኪያረጋግጥና የነፃነቱ ባለቤት እስኪሆን ድረስ እያንዳንዱ ትዉልድ (በየትዉልድ ዘመኑ) ከፊቱ የሚጋረጥበትን ወይም የሚያደናቅፈዉን እንቅፋት ታግሎ ማሸነፍ ተፍጥሯዊ ግዴታው ነው። በመሆኑም በተፈጥሮ ህግ እንደሚናጋ ስለምናውቅ ነው ጨለማን የማንፈራው ለማለት ነው። በእዉቀቱ ሥዩም ጠፈተህ፤ ጠፍተህ ከረመህ አሁን በዚች እጥር ምጥን ባለች ግጥምህ ብቅ ስላልክ ዴግሞ እንኳን ደህና መጣህ ለማለትም ጭምር ነው።

    Reply
  2. አትንኩት መላኩ says

    January 27, 2017 04:10 pm at 4:10 pm

    እውንትህን እግዚአብሔር። ይስ

    ጥህ እንዴት ትርድህው ባክህ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule