• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግጭት ምንቸት ውጣ የእርቅና የሰላም ምንቸት ግባ!!

September 11, 2015 07:19 am by Editor Leave a Comment

ከልብ በመነጨ፣ ፍጹም በሆነ የወገን ፍቅር በሶማሊያ በውትድርና ላሉ ወገኖች ፈጣሪ መፍትሄ እንዲሰጣቸው እንመኛለን። በማያውቁት ጉዳይ የበረሃ ጥሩር ለሚገርፋቸውና የነፍሳቸው ዋጋ በውል ለማይታወቀው ወገኖቻቸን እንኳን አደረሳችሁ ከማለት በላይ ሁሉም ወገኖች ድምጽ እንዲሆኗቸው እንጠይቃለን። በወር 30 ዶላር አበል ህይወታቸው ላለፈና አሁንም እያለፈ ለሚገኙት ሃዘናችን ትልቅ ነው። ትርጉም በሌለው ጦርነትና ለወደፊት ንጹሃን ዋጋ የሚከፈሉበት የፖለቲካዊ ቁማር ስትራቴጂ የደም ግብር ለመክፈል ሰልፍ ለያዛችሁ ፈጣሪ አሁንም ይድረስላችሁ!!

ለራባችሁም ለጠገባችሁም፡-

እንደ ልማዳችን እንኳን አደረሰን፣ አደረሳችሁ፣ እንቁጣጣሽ!! ስንል ለማለት ብቻ ባንለው ምንኛ ደስ ባለን ነበር። አዲሱን ዓመት ተቀብለን እልፍ ሳንል ባለንበት ቆመን ያረጅብናል። እኛም ያለ አንዳች ለውጥ ጎመን/አረም አሮብን የገንፎ ምንቸት ግባ እያልን በራሳችን እንደቀለድን እናረጃለን!! እኛና ዘመን እንዲህ ባለ ሂደት የጎንዮሽ እየነጎድን ነው። መለስ እንኳን ካለፉ ሦስት ዓመት አለፈ!! የክፋት ውርሳቸው ግን አሁንም አለ!!

ካሮጌውና ከጥንቱ ለመማር አንሞክርም። ያ ልባም አቀንቃኝ ቴዎድሮስ ካሳሁን “የኋላው ከሌለ የታለ የፊቱ” እንዳለው!! ምን ይህ ብቻ “የመጣንበት መንገድ ያሳዝናል” ሲል አእምሮን በርቅሶ በሚገባ የግጥም ፍሰት እየዘከርን ያለፍናቸውን ዓመታት ያመላክተናል። “አፈር ይዞ ውስጡ አረንጓዴ ለምን ይሆን የራበው ሆዴ?” እያለ “አመመኝ አመመኝ ውስጤን አመመኝ” ሲል የልቡን ስቃይ ያዜምልናል። አይገባንም። ወይም እንዲገባን አንወድም!! እውነትም አመመኝ!!

ነገሩ ሁሉ ተቃራኒ ነው። የመታደስ ፍንጭ አይታይም። ውሸቱ አይሏል። ስርቆቱ ጨምሯዋል። እንደ እንቁጣጣሽ በግና ዶሮ ዋጋ ከህደቱ ለከት አጥቷል። የሚልሱትና የሚቀምሱት አጥትው እንደጨለመባቸው ወገኖች ኅሊና የሚባለው የልቡና መብራት ተቃጥሏል፤ ጠፍቷል። ርሃብ ዘር ሳይለይ ወገኖችን እያራገፈ “የእድገት፣ የብልጽግና” ከበሮ ይደለቃል። ኅሊናቸው የቀረናባቸው “ዝናብን መቆጣጠር የቻለ አገር የለም” እያሉ የተላላኪነት ዕድሜያቸውን ያራዝሙብናል።

የአድርባይነት ተምሳሌት ተደርገው የተወሰዱት ገዢዎች የመከርቸሚያውን ሰንሰለት ከማላላት ይልቅ አደድረውታል። ዳክረው ዳክረው “የደኅንነት አገዛዝ” ትግራይ ላይ ተሰብስበው ቸንክረውብናል፤ የደኅንነት ሹሞች የአገዛዙ ቁንጮዎች ሆነዋል። “ባለ ራዕዩ መሪ” የመለመሏቸው የአፈና ማሽኖች “ውርስ ወይም ሞት” ብለው ተነስተዋል። እነርሱ አውራ ሆነው ሌሎችን ጫጩት በማድረግ ቀጥቅጦ ለመግዛት ተቧድነዋል።

ወግ ነውና በአዲስ ዓመት እንዲህ እንላለን። “አውራዎቹ” እጅግ ጥቂት፣ ጫጩቶቹ እጅግ ብዙ ናችውና ያጨለማችሁትን የልቡናችሁን መብራት አብሩት!! ለዕብሪታችሁ ገደብ አድርጉለት፤ ዓመት አልፎ ዓመት ሲተካ የትክክለኛነታችሁ ማረጋገጫ ሠርቲፊኬት ሳይሆን ምሬትን በአንድ ተጨማሪ ዓመት ማግዘፋችሁ ይታያችሁ፤ ሌሎችም ለአገራቸው የማሰብና አገራቸውን በራሳቸው የሰላም መንገድ የመውደድ መብት ይኑራቸው፤ ምሬት ጥላቻን፤ ጥላቻም በቀልን አርግዞ የግድ መውለድ የለበትም፤ የእርቅና የሰላም ምንቸት ገብቶ የግጭትና የጥላቻ ምንቸት እንዲወጣ ሁሉም ዓይነት መስዋዕትነት ይከፈል!! ኢትዮጵያችንም ትኑርልን። መጪው ትውልድም አገር አልባ አይሁን። ይመርብን።


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule