• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሥራ ፈላጊው” ገብረሕይወት አስማረ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በሕገወጥ መልኩ ሲያዘዋውር ተያዘ

July 25, 2019 10:07 pm by Editor 1 Comment

“ሥራ ፈላጊው” ገብረሕይወት አስማረ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በሕገወጥ መልኩ ሲያዘዋውር ተያዘ።

“ገንዘቡ የተያዘው ሐምሌ 14/2011 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ገዳማ ከጠገዴ ወረዳ ሾርካ ንዑስ ወረዳ መፈተሻ ኬላ ላይ ነው” ብሏል ፖሊስ ለአብመድ በሰጠው መረጃ። በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ዋና የሥራ ሂደት ባለቤት ምክትል ኮማንደር አስማማው ካሴ እንደገለጹት አቶ ገብረሕይወት አስማረ የተባለ ተጠርጣሪ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በቦርሳ ይዞ ሲንቀሳቀስ በቁጥጥ ሥር ውሏል።

የተጠርጣሪው መታወቂያ “ሥራ ፈላጊ” የሚል መሆኑንም ነው ምክትል ኮማንደር አስማማው የተናገሩት፡፡ ግለሰቡም ከጎንደር ወደ ሁመራ ተጓዥ እንደነበር መናገሩም ተሰምቷል። ከ110 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በተጨማሪ የእንግሊዝ ፓውንድ መገኘቱንም ነው የወንጀል ምርመራ ዋና የሥራ ሂደት ባለቤቱ ያመለከቱት።

ከጎልጉል ዝግጅት ክፍል፥ መቶ አሥር ሺህ ዶላር በብር ሲመለስ በርከት ያሉ ሚሊዮኖች ይሆናል። ይህ ዓይነቱ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር እጅግ ከመስፋፋቱ የተነሳ ይህ ሁሉ ገንዘብ የሚመጣው ከየት ነው? ዋንኛ አስተላላፊዎችስ እነማን ናቸው? የሚል ጥያቄ ያስነሳል። አገር በማፍረስ ዓላማ ላይ ትጋት እያደረጉ ያሉ በዚህ ዓይነቱ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ውስጥ እንዳሉበት አጠያያቂ አይደለም፥ በተለይ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው የሃሰት ዜና የዚህ ዓይነቱ ሤራ ውጤት መሆኑ አይጠረጠርም። በርግጥ ገንዘቡ መያዙ መልካም ሆኖ ሳለ ምንጩን ማድረቅ ግን በቅድሚያ የመንግሥት ኃላፊነት ነው። የሕዝቡንም የማያቋርጥ ድጋፍ ይጠይቃል።

©አብመድ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Gi Haile says

    July 27, 2019 06:12 am at 6:12 am

    የግለሰቡን የግንኙነት መዋቅር በምርመራ መበጣጠስ አስፈላጊ ከዚህ ሰው ጋር የሚሰሩትን ሁሉ በቁጥጥር ስር መዋል ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule