የፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ህግ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣናት እና ግብረ አበር ባለሀብቶች ላይ የመሰረተውን ክስ በፍርድ ቤት ማሰማት ጀምሯል። የኮሚሽኑ ዐቃቤ ህግ በተለይም በአንደኛው ተከሳሽ በአቶ መላኩ ፈንታ ላይ መዝገብ ቁጥር 14356 ስር ባለው 11ኛ ክስ ውስጥ ተከሳሹ በትዳር ያለችን ሴት አስኮብልለዋል የሚል ክስ መስርቶባቸዋል። ትናንት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ክሱ ሲነበብ፤ 1ኛው ተከሳሽ አቶ መላኩ ፈንታ የስራ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ለስራ ጉዳይ የመጣችን ሴት፤ ትዳሯን ፈታና በትዳር ውስጥ ያፈራቻቸውን ሦስት ልጆች በትና አብራቸው እንድትሆን አድርገዋል ሲል ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ሲል ከሷቸዋል። ወ/ሮ መቅደስ ለማ የተባሉት እኚሁ ሴት የቀድሞ ባለቤታቸውን ንብረት … [Read more...] about በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ
Law
የሕግ ያለህ
አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!
‹‹ ዲሞክራሲ የሚመሠረተው መንግስት ሕዝቡን ሊያገለግል የቆመ ነው በሚል መሠረት ሃሳብ ላይ ነው፡፡ ይህም ማለት ሕዝብ መንግሥትን ለማገልገል የተፈጠረ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር ህዝብ የአንድ ዲሞክራሳዊ አገር ዜጋ እንጂ ተገዥ አይደለም፡፡ መንግስት የህዝብን መብት በሚያስጠብቅበት ወቅት ህዝብ ደግሞ በልዋጩ ለመንግስት ታማኝነቱን ይገልፃል፤በጨቋኝ ሥርዓት ግን መንግስት ራሱን ከህዝብ በማግለል ታማኝነትን ከህዝብ ይሻል ፤መንግስት ውሳኔ የሚወስነው ተገቢውን የህዝብ ድጋፍና ተሳትፎ ሳያገኝ ከሆነ የህዝብ ታማኝነት መመኘት ከንቱ ቅዠት ይሆናል፡፡ ›› (what is democracy) ከሚለው መፃፍ የተወሰደ ነው፡፡ ጥላቻ ሁለተኛ ከባዱ የሰው ልጅ ስሜት ነው፤ፍቅር የመጀመሪያ ነው፡፡ ጥላቻ በፍራቻ በእውቀት ማነስና በተጠራጣሪነት የሚመጣ ነው፡፡ ጥላቻ ይቅር ባይነትና መግባባትን ያሣጣል፡፡ … [Read more...] about አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!
ጥያቄው ሃይማኖታዊ ነፃነት መብት ወይስ ፖለቲካዊ…
‹‹መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሃይማኖትም በመንግስት ጣልቃ አይገባም፡፡›› ሕገ መንግስት አንቀጽ 11 ንዕስ አንቀፅ 3፡፡ ‹‹ማንኛውም ሰው የማሰብ፤ የሕሊና እና የሃይማኖት ነጻነት አለው፡፡ ይህ መብት ማንኛውም ሰው የመረጠውን ሃይመኖት ወይም እምነት የመያዝ ወይም የመቀበል ሃይማኖቱንና እምነቱን ለብቻ ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን በይፋ ወይም በግል የማምለክ፣ የመከተል፣የመተግበር፣ የማስተማር ወይም የመግለጽ መብትን ያካትታል፡፡›› ሕገ መንግስት አንቀጽ 27 ንዕሱ አንቀፅ 1፡፡ ‹‹ማንኛውም ሰው የሚፈልገውን እምነት ለመያዝ ያለውን ነጻነት በኃይል ወይም በሌላ ሁኔታ ማስገደድ ወይም መከልከል አይቻልም፡፡›› ሕገ መንግስት አንቀጽ 27 ንዕስ አንቀፅ 3 ፡፡ የሙስሊሞች ጥያቄ 1ኛ. በስልጣን ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች … [Read more...] about ጥያቄው ሃይማኖታዊ ነፃነት መብት ወይስ ፖለቲካዊ…
አጭር ማስታወሻ በሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሠልፍ
ነሀሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ መጥራቱ የሚታወቅ ነው፤ ይሁን እንጂ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት እንደሰፈር ጉልበታኛ ዱንኳን ሰባሪ ዘው ብሎ በሃይማኖት ስበብ ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ቀንና ሰዓት እንዲሁም ቦታ በህግ አግባብ ሣይሆን በጉልበት ሠልፍ መሰል ሠልፍ ማካሄዱ የሚታወቅ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም የተቃውሞ ሠልፍ በማድረግ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የተቃውሞ ሠልፈኞች እንዲሁም የአገር ውስጥና የውጪ የመገናኛ ብዙሃን በተገኙበት መንግስት ሊመልሳቸው የሚገባ ጥያቄዎችን የጠየቀ ሲሆን ለጥያቄዎቹም ምላሽ የሰጠው የጊዜ ገደብ ሦስት ወር መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ መንግስት በተሰጠው ጊዜ የተጠየቀውን ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ፓርቲውን በመወንጀል እና ስም የማጥፋት ዘመቻውን አጠናክሮ … [Read more...] about አጭር ማስታወሻ በሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሠልፍ
የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ
* አቶ በእግዚአብሔርና አቶ ምሕረተአብ ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው * ሦስት የባለሥልጣኑ ሠራተኞች በነፃ ተሰናበቱ * የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ስምንት የክስ መዝገቦች አቅርቧል የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በከባድ የሙስና ወንጀል ተሳትፎ በጠረጠራቸውና ከሦስት ወራት በላይ በእስር ላይ ባቆያቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞች፣ ነጋዴዎችና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ክስ መመሥረቱን፣ ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም፣ ተጠርጣሪዎቹ መከሰሳቸውን የሚያሳይ ክስ እንዳልደረሳቸውና የሕግ ሥርዓትን ያልተከተለ መሆኑን በመግለጽ ክሱን ተቃወሙ፡፡ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራውን አጠናቆ ለኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ማስረከቡን፣ ጊዜ ቀጠሮውን ሲከታተል ለነበረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ … [Read more...] about የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ
ከፍተኛ ዋጋ ያለው የሊዝ መብት በተጭበረበረ መንገድ በማሸጥ የተጠረጠሩ ባልና ሚስት ታሰሩ
ፈጽመዋል በተባሉት በዋና ወንጀል አድራጊነት፣ በአታላይነት፣ በከባድ እምነት ማጉደል፣ በሰነድ ማጥፋትና ሐሰተኛ ምስክርነት መስጠት ወንጀል የተጠረጠሩት ባልና ሚስት፣ አቶ ጌታቸው ጣሰውና ወይዘሮ ሸዋነሽ መንግሥቱ፣ እንዲሁም የቅርብ ዝምድና እንዳላቸው የሚገለጸው አቶ ዘውዱ ክንፈና አቶ ወንድአፍራሽ ፍቅሩ፣ ከፍተኛ ዋጋ ያለውን የሊዝ መብት፣ በተጭበረበረ መንገድ እንዲሸጥ አድርገዋል በሚል ታሠሩ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመዋል በተባሉባቸው ድርጊቶች ስድስት ክሶች የተመሠረቱባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሲሆን፣ የፈጸሙት ወንጀል በዝምድና በተሳሰረ መንገድና ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ ዋስትና ከልክሏቸው፣ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ብይን ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመዋል የተባሉባቸው የወንጀል ድርጊቶችን በሚመለከት ክስ ያቀረበባቸው የፌዴራል … [Read more...] about ከፍተኛ ዋጋ ያለው የሊዝ መብት በተጭበረበረ መንገድ በማሸጥ የተጠረጠሩ ባልና ሚስት ታሰሩ
በግብረሰዶም ተጠርጣሪዎች ላይ የሳይኮሎጂና የሳይካትሪ ባለሙያ የምስክርነት ቃል ሰጡ
ሁለት የ10 እና የ11 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የአራተኛና የአምስተኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ የግብረሰዶም ጥቃት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ ስድስት መምህራን ክስ ላይ፣ ከዓቃቤ ሕግ ምስክሮች በተጨማሪ አንዲት የሳይኮሎጂና የሳይካትሪ ባለሙያ ሐምሌ 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው የሙያ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጡ፡፡ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የመሠረተውን የወንጀል ክስ በማየት ላይ ያለው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሰባተኛ የወንጀል ችሎት፣ ስማቸው በሚዲያ እንዳይገለጽ የከለከለላቸው የሳይኮሎጂስትና የሳይካትሪ ባለሙያዋ፣ በተጠርጣሪ መምህራን የግብረሰዶም ጥቃት ደርሶባቸዋል የተባሉትን ሁለት ወንድ ሕፃናት፣ ለሦስት ጊዜያት አግኝተው እንዳነጋገሯቸው ገልጸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹንም ሆኑ የጥቃቱ ሰለባ ናቸው የተባሉት … [Read more...] about በግብረሰዶም ተጠርጣሪዎች ላይ የሳይኮሎጂና የሳይካትሪ ባለሙያ የምስክርነት ቃል ሰጡ
ግብረሰዶም ፈጽመዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮች ተሰሙ
ከአዘጋጆቹ፤ ኢህአዴግ የፈጠራትና “በሕዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሠረተችው” ኢትዮጵያ ይህንን ትመስላለች፡፡ ሰላማዊ ሰዎችን “አሸባሪ” እያሉ ለማሰር ሕግ ከማውጣትና ዜጎችን በፍርሃት ከመሸበብ ይልቅ እንዲህ ያለው አስጸያፊ ተግባር በህጻናት ላይ ከመፈጸሙ በፊት እጅግ ከረር ያሉና ቅጣታቸው የከበደ ሕጎችን ማውጣት፤ የማኅበረሰቡ ድርና ማግ የሆኑትን እና ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን የሚያደፋሩ አማራጮችን መፍጠር፤ ወዘተ ጥቂቶቹ የመከላከያ አማራጮች ናቸው፡፡ ይህ በአንድ ት/ቤት የተፈጸመና ይፋ የሆነ ነው እንጂ በየጊዜው በተመሳሳይ ሁኔታ እየተደፈሩ ተበላሽተው የቀሩ ልጆች ስንት እንደሆኑ ለማወቅ አንዱ ህጻን እዚሁ ዜና ላይ እንደተናገረው ከሌሎች አራት ት/ቤቶች ተደፍሮ መጥቶ ወደዚህኛው (ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ) ከገባ በኋላም ተመሳሳይ ጥቃት እንደተሰነዘረበት ማንበቡ ከበቂ በላይ ማስረጃ … [Read more...] about ግብረሰዶም ፈጽመዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮች ተሰሙ
የአደባባይ የብልግና ቧልት በሕጉ እንዴት ይታያል?
የዛሬው ጽሑፍ የሚያጠነጥነው በወንጀል ሕግ ዙሪያ ነው፡፡ የወንጀል ሕግና የኅብረተሰቡ የሞራል አስተሳሰብ የጠበቀ ቁርኝት አላቸው፡፡ በአብዛኛው በኅብረተሰቡ እንደ ኃጢአት ወይም ነውር የሚቆጠሩ ድርጊቶች በወንጀል ሕግም የሚያስጠይቁ ናቸው፡፡ አመንዝራነት፣ ስርቆት፣ ስድብ፣ ግብረ ሰዶም ወዘተ. ኃጢአት ወይም ነውር ብቻ ሳይሆኑ ወንጀልም ተደርገው በወንጀል ሕጉ እንደሚያስቀጡ ተመልክቶ እናገኛለን፡፡ ይሁን እንጂ ኃጢአት ወይም ነውር የሆነ ድርጊት ሁሉ ግን ወንጀል ላይሆን ይችላል፡፡ ዝሙት አዳሪነትን ለዓብነት ብንመለከት ድርጊቱ ኃጢአት ወይም ነውር መሆኑ ባያጠያይቅም፣ በወንጀል ሕጋችን በመርህ ደረጃ የወንጀል ኃላፊነት የማያስከትል ድርጊት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ የወንጀልና የኃጢአት ግንኙነት ስፋት እንደ ኅብረተሰቡ የሞራል አስተሳሰብ የሚለያይ ስለሚሆን በሁሉም ዘንድ ተመሳሳይ መግባባት ላይኖር … [Read more...] about የአደባባይ የብልግና ቧልት በሕጉ እንዴት ይታያል?
Harmony among Ethiopian various legislative frameworks
In this article I will attempt to examine whether or not Ethiopia as a federal state structure has put in place all necessary mechanisms so that it functions as it supposed to do so. Practical examples in other countries constituted as federal political state structure will be cited repeatedly to give our readers a full grasp of the complex legal issues at hand. This is in particular important for those who are not legal trained and find difficulty to understand the legal question at hand. In … [Read more...] about Harmony among Ethiopian various legislative frameworks









