• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ማስፈጸም አይችልም

July 13, 2013 01:49 am by Editor 1 Comment

“ዕድገት”፣ “ትራንስፎርሜሽን”፣ “ህዳሴ”፣ “የመለስ ውርስ (ሌጋሲ)”፣ … በሚመሯት ኢትዮጵያ ሙስና እየከፋ መሄዱ ታወቀ፤ ከመቶ ሰዎች ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት ጉቦ የሚሰጡ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡

ሰሞኑን ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት (Transparency International) ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በርካታ የአፍሪካ አገራት በሙስና “መበስበሳቸውን” ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ አገራት መካከል እንደምትገኝ ዘግቧል፡፡

ከዚህ በፊት በያዝነው ዓመት ጥር ወር የሙስና አደጋ የተጋረጠባቸው አገራትን ዝርዝርና የአደጋውን መጠን በሰባት ደረጃ በመከፋፈል ይኸው ድርጅት ባወጣበት ጊዜ ኢትዮጵያን በከፍተኛ የሙስና አደጋ ውስጥ ከሚገኙ አገራት ዝርዝር ውስጥ አስገብቷት ነበር፡፡ በዚህ ዘገባ መሠረት በሙስና የተዘፈቁትን አገራት በመከፋፈል ባስቀመጠው ባለዘጠኝ መዘርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛው ውስጥ አካትቷታል፡፡

bribe 1ሰሞኑን የወጣው ዘገባ ይህንን እንዲል ያስቻለው አንዱ መረጃ “ጉቦ ሰጥተዋል ወይ (ያውቃል)?” በማለት ለአንድ ሺህ ሰዎች ያቀረበውን ናሙና መሠረት በማድረግ ነው፡፡ በጥያቄው መሠረት በኢትዮጵያ 44በመቶው “አዎን” በማለት መመለሳቸውን ዘግቧል፡፡

ጥናቱ የ3በመቶ የስህተት ገደብ ያደረገ ቢሆንም፤ የነጻ ሚዲያ፣ በነጻነት የመናገር፣ ያለፍርሃትና ዛቻ ሃሳብን የመግለጽ፣ ወዘተ መብት በተረገጠባት ኢትዮጵያ የዘገባው ቁጥር ከዚህ በላይ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፡፡ በቅርቡ ራሱ ኢህአዴግ በሙስና ላይ ዘመቻ ጀምሬያለሁ በማለት የወሰደው እርምጃ ጎልጉል “ሙስናን በስንጥር” በማለት የዘገበው ቢሆንም ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት ካወጣው መረጃ ጋር ሲነጻጸር “የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቀውንና የሚኖረውን ብታውቁና ብትኖሩ ኖሮ” የሚያስብል ነው፡፡

ከህዝቧ ግማሽ በላይ ሥራአጥ በሆነባት (የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ነው)፣ 86በመቶ ምንጥ ያለ ድሃና 80በመቶ በግብርና የተሰማራ ችግረኛ ሕዝብ በሚኖርባት አገር፤ ዘገባው ያወጣው አኃዝ ጉዳይ ከሚያስፈጽመው ሕዝብ መካከል ግማሽ ያህሉ ጉቦ መስጠት ግዴታው መሆኑ፤ ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ለማስፈጸም ጨርሶ አቅቶታል ወይም ጉዳዩን ከማስፈጸም ተቆጥቧል የሚያስብል ነው፡፡

ለ5ዓመታት በአዲስአበባ ኃላፊነት ከቆዩ በኋላ ሰሞኑን ወደ ጠ/ሚ/ር ጽ/ቤት “ማቀዝቀዣ” የገቡት ኩማ ደመቅሳ በስንብታቸው ወቅት በኢህአዴግኛ “ኪራይ ሰብሳቢነት” አሁንም የከተማዋ አሳሳቢ ችግር እንደሆነ አምርረው ተናግረዋል፡፡ ይህ ሁኔታና አሁን የወጣው ዘገባ “ውርሳቸውን እናስጠበቃለን” የሚባሉት ሟቹ መለስ፤ በረሃ በነጻአውጪነት ከዚያም በመንግሥትነት ራሳቸው ስለመሩት ድርጅት የተናገሩትን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት “ከእንጥላችን ገምተናል”!

(የዘገባውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Liberalism says

    July 26, 2014 03:49 pm at 3:49 pm

    Liberalism

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule