• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር

September 16, 2016 11:58 pm by Editor 2 Comments

የአፍሪካ ነፃነት አብሪ ኮከብና  በጀግና ህዝቧ አኩሪ ተጋድሎ ባለክብር የነበረቺው ኢትዮጵያ ዛሬ  በከፋ ፈተና ውስጥ ገብታለች። በብርቱ ትግልና ጥንቃቄ መወገድ ያለባቸው ያገርና የህዝብ ደህንነት ስጋቶች ከፊቷ ተጋርጠዋል። የርስ በርስ ጦርነት ስጋት፣ የአስተማማኝና ዘላቂ ሰላም እጦት፣ የማእከላዊ መንግስት አቅጣጫ ብዥታና የውጭ ጠላት ስጋት፣ ጥቂቶቹ ናቸው። እነዚህንና መሰል ያገርና ህዝብ ደህንነት ስጋቶች ለማስወገድና ጤናማ የፖለቲካ ድባብ ለመፍጠር ባስቸኳይ መንቀሳቀስና ሀገርና ህዝብን ካሳፋሪ ውድቀት ማዳን ያስፈልጋል።

በኢትዮጵያና ህዝቧ ላይ ያንዣበቡትን  እነዚህን  አደጋዎች ማስወገድ የሚቻለው እንዴት ነው? በእርግጥስ ይቻላል?

እነዚህን ያገርና የህዝብ ህልውና ፈተናዎች በማስወገድ የኢትዮጵያን ሁኔታ ሰላማዊ አቅጣጫ እንዲይዝ ማድረግ የሚችለውስ ማነው? የሁሉም ጥያቄዎች መልስ አዎንታዊ ነው፤ መሆንም አለበት። ሃላፊነቱም የሁሉም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎችና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ነው። በዚህ ፈታኝ የታሪክ ወቅት በየጎራው የተሰለፉት የኢትዮጵያ ልጆች የገዛ ሀገራቸውንና  ህዝቧን የማዳን ታሪካዊ ሃላፊነት መሸከም አለባቸው።

ስራው መጀመር ያለበት መቼ ነው?

ኢትዮጵያ በሰላምና ፀጥታ ፈተና ላይ ወድቃለች፤ ግጭቱም ከሯል፤ በየለቱ የሰው ህይወት እየጠፋ ነው። እናም ችግሩ አጣዳፊ ነው። ጊዜ የሚሰጥ አይደለም። ቀናት በተቆጠሩ ቁጥር አደጋዊ እየሰፋና መልኩን እየለወጠ ችግሩን ለመፍታት የማይቻልበት ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል። ስለሆነም ስራው ዛሬ  ነገ ሳይባል ባስቸኳይ መጀመር አለበት።

ኢትዮጵያና ህዝቧን ካደጋ የማዳን ስራው  እንዴት ሊጀመር ይችላል? ስልትና ብልሃቱስ ምንድነው?

ኢትዮጵያን ከገጠማት የወቅቱን ጭንቅ ለማውጣት መንገዱ አንድ ብቻ ነው። ይሄውም መነጋገር ነው። በየጎራው ያሉት የኢትዮጵያ ልጆች ተሰባስበው መነጋገር አለባቸው። ከዚህ ስብሰባ የሚቀር ወገን ወይም ቡድን ሊኖር አይገባም። በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሃይሎች ሁሉ በዚህ የምክክርና ክርክር መድረክ ላይ መገኘት አለባቸው። የትኛውም ወገን ምንም አይነት የፖለቲካ አቋም ወይም ሃሳብ ይኑረው በዚህ ፋታ በማይሰጥ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ይሳተፍ ዘንድ ወቅቱ የግድ ይላል። እናም ጥሪው ያለምንም ልዩነት ለኢትዮጵያዊያን የፖለቲካ ሃይሎች ሁሉ ነው። ኢትዮጵያን ለማዳን መፍትሄው ባስቸኳይ መሰባሰብና መምከር ነው። አማራጭ መንገዶችን በጋራ ለመፈለግና በሚያዋጣው መንገድ ላይ ለመስማማት መነጋገር ያስፈልጋል። ባጠቃላይ ኢትዮጵያን ለማዳን ከመነጋገር የተሻለ መንገድ የለም። የኢትዮጵያ ቀጣይ መንገድ ምንድነው በሚለውም ሆነ አሁን ከገባችበት ማጥ ማውጣት የሚቻለው እንዴት ነው በሚሉት ጥያቅዎች መልስ ላይ ለመስማማት መመካከር ጠቃሚ ብቻ ሳይሆን ወሳኝ ነው።

የምክክሩና ክርክሩ ፋይዳ

1. ሳይነጋገሩ ሰላም ማምጣት አይቻልም።

2. ሳይነጋገሩ ችግሩን መፍታት አይቻልም።

3. ሳይነጋገሩ  ወደፊት መራመድ አይቻልም

4. ሳይነጋገሩ፣ ሳይከራከሩና ሳይስማሙ መፍትሄ ማምጣት አይቻልም። ስለሆነም የምክክሩና ክርክሩ መድረክ ከወቅቱ ጭንቅ መውጫ በር የሚከፍት ስለሆነ ወሳኝ መድረክ ነው።

መድረኩን የሚፈጥረው ማነው? ስፍራውስየት ነው?

ይህን ታላቅ ሃላፊነት ለመውሰድ የተዘጋጀው ፥ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ፥ የተባለው ግብረሰናይ ድርጅት ከኢትዮጵያ ህዝብ ወዳጆችና የሰላም ሀይሎች ጋር በመተባበር ነው። ስፍራውም በዋሽንግተን ዲሲ አሜሪካ ይሆናል።

“ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ” ማነው?

ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ (peace and Justice for Africa) የአፍሪካ አህጉር የሰላም ምድር እንዲሆንና የህግ የበላይነት የበለፀገ የህዝብ ባህል እንዲሆን ለመታገል በአሜሪካ ህግ መሰረት የተቋቋመ ገለልተኛ ግብረሰናይ ድርጅት ነው። ድርጅቱ ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ እድገት ብቻ ሳይሆን ለህልውናዋም ወሳኝ ቅድመሁኔታዎች ናቸው የሚል እምነት ባላቸው ኢትዮጵያውያንና ሌሎች አፍሪካውያን የተመሰረተ ነፃና ገለልተኛ ድርጅት ነው። ዋና ፅህፈት ቤቱ በዋሽንግተን ዲሲ ሲሆን በየአህጉሩ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶችን ከፍቶ ለመንቀሳቀስ ሰፊ እቅድ ይዟል። የመጀመርያውን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በካናዳ  ከፍቷል። ባሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የገጠማትን ከባድ የሰላምና ጸጥታ ችግር በመመልከት ለጉዳዩ ቀዳሚ ትኩረት በመስጠት መፍትሄ በማፈላለጉ ሂደት የበኩሉን እገዛ ለማድረግ ሌት ተቀን ያለረፍት እየሰራ ነው። ለጥረቱ ስኬት የኢትዮጵያንና ህዝቧን  ደህንነት የሚሹ አካላትን  ሁሉ ድጋፍ ይሻል።

የታቀደው ውይይትና ክርክር መድረክ  ይዘትና ቅርፅ ምን ይመስላል?

በዚህ ወሳንና ሰፊ መድረክ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሀይሎች ሁሉ እንዲሳተፉ ይጠበቃል። ታዛቢዎችና የልማት አጋሮችም ተሳታፊ ናቸው። የአፍሪካ ህብረት፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአሜሪካና የሌሎችም መንግስታት ተወካዮች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

የውይይትና ክርክር መድረኩ አላማ ምንድነው?

መድረኩ በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ይመክራል።

ኢትዮጵያ አሁን ከገባችበት አጣብቂኝ መውጫው መንገድ ምንድነው? ምን መደረግ አለበት?

ቀጣዩ ጉዞስ ወዴት ነው?

አማራጮች ምንድናቸው?

ከገባንበት አጣብቂኝ እንዴት እንውጣ?

ያለግጭት ገደሉን እንዴት እንሻገር?

የእርስ በእርስ ጦርነት ስጋት ማስወገጃው ስልት ምንድነው?

ሁሉንም የሚያስማማው መንገድ ምንድነው?

ሁሉንም የሚያስማማስ መንገድ አለ?

ኢትዮጵያን ለማዳንንና ጦርነትን ለማስወገድ ከመነጋገር ሌላ ምን መንገድ አለ?

እነዚህ ጥያቄዎች ለመነሻነት የቀረቡ ናቸው። ተሳታፊዎች የራሳቸውን አካሄድና አጀንዳም ሊቀርፁ ይችላሉ። ከላይ በተነሱት ጥያቄዎች ላይ የሚሰጡት መልሶችም የተለያዩ ናቸው። ሁሉም ወገኖች የሚሰጡት መልስና የሚያቀርጉት ሃሳብ ይለያያል። የመፍትሄ ሃሳቦችም ይለያያሉ። ልዩነቱ ከሃይል ሌላ ለኢትዮጵያ ሰላም ሊያመጣ አይችልም እስከሚል ድረስ ይዘልቃል። የመድረኩ አዘጋጅ ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ በየትኛውም አማራጭ የፖለቲካ መፍትሄ ላይ የራሱ አቋም የለውም። ሆኖም በየትኛውም አማራጭ ስልት ላይ ለመስማማት ከመነጋገር ሌላ መንገድ እንደሌለ በፅኑ ያምናል። ከዚህም ሌላ መቼም ቢሆን ሰላምን በሰላም ለማምጣት እስከተቻለ ድረስ ለሰላማዊ ንግግርና ክርክር ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል የሚለውን ሃሳብ በሙሉ ልብ ይደግፋል። በመጨረሻም ይህ መድረክ የትግል ጥሪ ሳይሆን ኢትዮጵያን ከአደጋ ለማዳን የሁሉም ፖለቲካ ሀይሎች አማራጮች የሚመረመሩበትና የሚሞገቱበት በማጠቃለያውም ተስማሚ ነው የተባለው የሰላም እስትራትጂ ተግባራዊ የሚሆንበት አቅጣጫ የሚነደፍበት መድረክ እንደሚሆን ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል።

ስለዚህ ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ የመድረኩን አስፈላጊነት በውል በማጤን ለስኬቱ ከጎናችን እንዲቆሙ፣ ማንኛውንን ትብብርም እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። በታቀደው የሰላም መድረክ ለመሳተፍ ፍላጎት ያላችሁ ሁሉ አቋማችሁን ብታሳውቁን ለዝግጅት ይረዳናል። አማራጭ መፍትሄም ሆነ ምክር ወይም አስተያየት ያላችሁ ወገኖች ሁሉ ከዚህ በታች በተገለፀው የድርጅታችን አድራሻ ብትልኩልን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው። ስለመድረኩ ዝግጅትና ይዘትም የተሻለ አማራጭ አለን የምትሉ ሃሳባችሁን ብትልኩልን ለእቅዱ ስኬት ይበጃልና በደስታ እንቀበላለን።

ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ (Peace and Justice for Africa)

840 First Street NE,
Washington DC, 20002
Email: Peaceafrica16@gmail.com
Telephone: Office: 202-380-3600
Fax: 202 2896539
Direct mobile phone: 703-798-1156
Website: www.peaceandjusticeforafrica.org

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    September 23, 2016 11:00 pm at 11:00 pm

    Please say no to the fascists from TIGRAI. We are not short of organizations but we need unity and action to dismantle the home grown fascists.

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    September 25, 2016 03:24 am at 3:24 am

    ጓዶች!! ያልሆነ ህልም አታልሙ!! ቅዠት!!ቅዠት! ሃገሪቱ ደህና ናት!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule